Dejen Polytecnic College

Dejen Polytecnic College Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dejen Polytecnic College, College & University, dejen, Dejen.

የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአንድነት እና የጋራ መግባባት ፕሮግራም“አብሮ የበላን ጷግሜ አይሽረውም!”የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተቋሙን አንድነት ይበልጥ ለማጠናከር እና የጋራ የሥራ ስሜትን...
29/05/2026

የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአንድነት እና የጋራ መግባባት ፕሮግራም
“አብሮ የበላን ጷግሜ አይሽረውም!”

የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተቋሙን አንድነት ይበልጥ ለማጠናከር እና የጋራ የሥራ ስሜትን ለመገንባት የሚያስችል የ “ጌት ቱጌዘር” (Get-together) ፕሮግራም ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም አካሂዷል።
የፕሮግራሙ ዋና ዋና ዓላማዎች፦

ተቋማዊ አንድነትን መፍጠር፦
በሠራተኞች መካከል ያለውን መተማመን እና የመቀራረብ ስሜት ማሳደግ።
የስትራቴጂ ግብ መምታት፦ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂን በኮሌጃችን ውጤታማ በሆነ መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ የጋራ መግባባት ላይ መድረስ።
የሥራ ተነሳሽነት፦ በአብሮነት የሚመነጨውን የሥራ ጥራት እና ውጤታማነት ከፍ ማድረግ።

ይህንን ጠቃሚ የጋራ ልብ ለማሳካት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ታምኖበታል።

27/05/2026
የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለላቀ የትምህርት ጥራትና ዲጂታላይዜሽን ቅድሚያ ሰጥቷል::የደጀን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውስጥ ጥራት አረጋጋጭ ቡድን ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሁለት ቁልፍ የቴክኒክና ሙያ ስ...
26/05/2026

የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለላቀ የትምህርት ጥራትና ዲጂታላይዜሽን ቅድሚያ ሰጥቷል::

የደጀን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውስጥ ጥራት አረጋጋጭ ቡድን ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሁለት ቁልፍ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አጀንዳዎች ማለትም በሱፐርቪዥንና ኢንስፔክሽን እንዲሁም በዲጂታል ቤተ መጽሐፍት እሳቤዎች አደረጃጀትና አጠቃቀም ዙሪያ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል።

ኢንስትራክተር ካሳሁን ወንድሙ ባቀረቡት ሰነድ፡
የሱፐርቪዥንና ኢንስፔክሽን ዓላማዎች፣ የባለሙያ ሥነ-ምግባር እና መርሆች፣
የእነዚህ ሁለት ተግባራት አንድነትና ልዩነት፣
የዲጂታል ቤተ መጽሐፍት አስፈላጊነትና ውጤታማ የቤተ መጽሐፍት ባህሪያት በዝርዝር ቀርበዋል።

በመድረኩ የተገኙት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ይትባረክ ገነት፣ ስልጠናው የኮሌጁን ጥራትና ደረጃ ለማሳደግ ያለውን ፋይዳ በመጠቆም፣ የኮሌጁን አቅም ለመገንባት እና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመውጣት በሙያዊ ብቃት መታጠቅና የውስጥ አቅምን ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም ኮሌጁ ራሱን የቻለ ገቢ ማስገኘት እንዲችልና ከበጀት ጥገኝነት ለመላቀቅ የውስጥ አረጋጋጭ ቡድኑ እና መላው የኮሌጁ ማህበረሰብ በትኩረት እንዲሠሩ መልእክት አስተላልፈዋል።
በዕለቱ ከተሳታፊዎች የተነሱት ገንቢ ሀሳቦች ኮሌጁን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር የሚረዱ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ መድረክ ለኮሌጁ ቀጣይ የትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ጉዞ ትልቅ አቅም የፈጠረ ሆኗል።

ግንቦት 18/2018ዓ.ም
ደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብግንኙነትና ኮሙኒኬሽን

ደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ አባይ ስሚንቶ የእግርኳስ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ተካሄደ።///// # # # # # # # #//////የጨዋታው ዋና ዋና ሁነቶችብርቱ ፉክክር፦ ሁለቱም ቡድኖች ፈታኝ እና...
17/05/2026

ደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ አባይ ስሚንቶ
የእግርኳስ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ተካሄደ።
///// # # # # # # # #//////
የጨዋታው ዋና ዋና ሁነቶች

ብርቱ ፉክክር፦ ሁለቱም ቡድኖች ፈታኝ እና ወጣገባ በሆነው የሳር ሜዳ ላይ ጠንካራ ፉክክር ያደረጉበትና ከፍተኛ ጉልበት የታየበት ጨዋታ ነበር።

በንቅናቄ የተሞሉ ቅፅበቶች፦ በሁለቱም በኩል ተጫዋቾች ኳስ ለማግኘት ሲታገሉ፣ ስልታዊ ቅብብሎችን ሲያደርጉ እና በተለይ በደጀን ፓሊ ቴክኒክ በኩል በጫና ውስጥ ሆነው ኳሱን ወደ ፊት ሲገፉ ብሎም በሙከራ የታጀበ ጨዋታ አድርገዋል።

ጠንካራ የማጥቃት መስመር፦ አባይ ስሚንቶ በማጥቃት ረገድ ድንቅ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ በደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረብ ላይ 4 ጎሎችን በማስቆጠር ድሉን አረጋግጧል። ደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅም በበኩሉ 2 ድንቅ ጎሎችን አስቆጥሯል።

ይህ በዚህ እንዳለ የደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የእግርኳስ ቡድን መደበኛ ተግባራቸዉን እየከወኑ ጤናቸዉን ለመጠበቅ ከመጫወታቸዉ በዘለለ የኮሌጁን ገፅታ ለመገንባትና ኮሌጁ በማህበረሱ እንዲታወቅ የተሰራዉ ስራ ይበል የሚያስብል ነዉ እያልን ቡድኑ እዚህ እንዲደርስ በመጫወት ሞራል በመስጠት የተለያዩ የማልያና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ከፍተኛ ሚና ለተጫወቱ ድርጅቶች ና የኮሌጃችን አመራሮች እጅግ እናመሠግናለን።

ግንቦት 9/2018
ደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብግንኙነትና ኮሙኑኬሽን

በደጀን ከተማ ለ300 ሴቶች የሚሰጠው የማህበረሰብ አገልግሎት ስራ ሽግግር ስልጠና ተጀመረየደጀን ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ከ JHU-CCP SSPW Project ጋር በመተባበ...
11/05/2026

በደጀን ከተማ ለ300 ሴቶች የሚሰጠው የማህበረሰብ አገልግሎት ስራ ሽግግር ስልጠና ተጀመረ

የደጀን ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ከ JHU-CCP SSPW Project ጋር በመተባበር ከከተማው ለተውጣጡ 300 ስራ አጥ ሴቶች በማህበረሰብ አገልግሎት የስራ ሽግግር ላይ ያተኮረ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።
የስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሀብታሙ አየለ ስልጠናውን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት፤ ሰልጣኞች ለሁለት ቀናት የሚቆየውን ስልጠና በአፅንኦትና በትኩረት በመከታተል ለታለመለት ዓላማ ስኬት እንዲተጉ አሳስበዋል።

📘 የስልጠናው ዋና ዋና ዓላማዎች፦

በማህበረሰብ አገልግሎት ስራ ላይ የተሰማሩ ሴቶች ውጤታማና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማስቻል።
ተሳታፊዎች በማህበረሰብ አገልግሎት ላይ ያላቸውን ግንዛቤ በማሳደግ፣ የስራ ተነሳሽነትና ክህሎታቸውን ማዳበር።
በማህበረሰብ አገልግሎት አማካኝነት ሴቶች ወደ ቋሚ የስራ እድል እንዲሸጋገሩ ምቹ ሁኔታን መፍጠር።
በማህበረሰቡ ውስጥ የሚስተዋሉ ችግሮችን በስራ ተሳትፎ የመፍታት አቅምን ማሳደግ።
ይህ ስልጠና ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ በከተማው ውስጥ ያለውን ስራ አጥነት ለመቀነስና የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ታምኖበታል።

ደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብግንኙነትና ኮሙኑኬሽን

ከፍተኛ ፍጥጫ የነበረበትና የደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማስ እግርኳስ ቡድን ከጎጃም በር መሰናዶ ት/ቤት ጋር አቻ በመዉጣት  ወደ ጥሎ ማለፉ የተቀላቀለበት  ጨዋታ ተካሄዷል።ግንቦት 2 /201...
10/05/2026

ከፍተኛ ፍጥጫ የነበረበትና የደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማስ እግርኳስ ቡድን ከጎጃም በር መሰናዶ ት/ቤት ጋር አቻ በመዉጣት ወደ ጥሎ ማለፉ የተቀላቀለበት ጨዋታ ተካሄዷል።

ግንቦት 2 /2018 ዓ.ም

፦📍 ደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅየደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤቶች የቀሪ ወራትን ዕቅድ ለማሳካት በቅንጅት ለመስራት ተስማሙዛሬ ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ...
08/05/2026


📍 ደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤቶች የቀሪ ወራትን ዕቅድ ለማሳካት በቅንጅት ለመስራት ተስማሙ

ዛሬ ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም የደጀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ የደጀን ከተማና የወረዳ የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የምክክርና የዕቅድ ግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

የመድረኩ ዋና ዋና ነጥቦች፡-

🚀 ቴክኖሎጂና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፦ በቀሪ ወራት ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን ለማፍራት ቴክኖሎጂዎችን ሰርቶ ማሳየት፣ የአብዢ ስልጠናዎችን መስጠትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በስፋት መተግበር።

🎓 ትምህርትና ስልጠና፦ ለአጫጭር ስልጠናዎች ትኩረት በመስጠት ወጣቶችን ወደ ሥራ ማሰማራት ላይ ትኩረት ይደረጋል።

🏆 ይህ በዚህ እንዳለ ኮሌጁ ከ ACT (American College of Technology) ጋር በመተባበር ላሰለጠናቸው 2540 ሰልጣኞች መካከል ለ2,100 ሰልጣኞች የፈጠረው የሥራና የገበያ ትስስር በትልቅ ስኬት ተነስቷል።
👏 ስለሆነም ይህንን ግዙፍ ተግባር በኃላፊነት መርተው ለውጤት ያበቁት የኮሌጁ ኢንስትራክተሮችና የ ACT ፎካሎች ባንታለም ዳኘ እና ሰለሞን መኩሪያው ከመድረኩ ተሳታፊዎች ከፍተኛ አድናቆት ተችሯቸዋል። ቀሪውን 20% ተግባርም በዚሁ ትጋት ለማጠናቀቅ መግባባት ላይም ተደርሷል።

📌 በአጠቃላይ የቀሪ ወራት ዕቅዶችን ከዞኑ አፈጻጸም ጋር በማመሳከርና በቅንጅት በመስራት ውጤታማ ለማድረግ የጋራ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብግንኙነትና ኮሙኑኬሽን

በደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ"ዲጂታል አማራ" የንቅናቄና የስልጠና ሳምንት በይፋ ተጀመረደጀን፤ ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ምየዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠንና ማህበረሰቡን በቴክኖሎጂ ለማበልጸ...
21/04/2026

በደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ"ዲጂታል አማራ" የንቅናቄና የስልጠና ሳምንት በይፋ ተጀመረ
ደጀን፤ ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም

የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠንና ማህበረሰቡን በቴክኖሎጂ ለማበልጸግ የታለመው የዲጂታል አማራ ኢኒሼቲቭ የግንዛቤ ማስጨበጫ፣ የምዝገባና የስልጠና ሳምንት በደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በልዩ ሁኔታ ተጀምሯል። ከሚያዚያ 13 እስከ 20/2018 ዓ.ም የሚቆየው ይህ የንቅናቄ ሳምንት፣ ሰፊ የማህበረሰብ ክፍሎችን የዲጂታል እውቀት ባለቤት ለማድረግ አልሞ እየተሰራ ይገኛል።

የመጀመሪያው ቀን ውሎ
የንቅናቄ ሳምንቱ በይፋ በተበሰረበት በዛሬው ዕለት (ማክሰኞ ሚያዚያ 13) ሁለት ዋና ዋና የሥልጠና መርሃ ግብሮች ተከናውነዋል፡-
ረፋድ ላይ፡ ለኮሌጁ ማህበረሰብ እና ለደጀን ወረዳ ስራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት ባለሙያዎች የግንዛቤ ፈጠራና ስልጠና ተሰጥቷል።
ከሰዓት በኋላ፡ ለደጀን ከተማ አስተዳደር ሁሉም ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ሰራተኞች በዲጂታል አማራ ፋይዳ ዙሪያ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ተሰርቷል።
ስልጠናው ቀደም ሲል የዲጂታል ዕውቀት ባላቸውና የ"አሰልጣኞች ስልጠና" (ToT) በወሰዱ የኮሌጁ አንጋፋ ኢንስትራክተሮች አማካኝነት እየተሰጠ ይገኛል።

የኮሌጁ ዲን አቶ ይትባረክ ገነት መርሃ ግብሩን በንግግር ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ ስልጠናው ከወቅቱ የቴክኖሎጂ ሽግግር ጋር አብሮ ለመራመድ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። ዲኑ ባስተላለፉት መልዕክት፡
"እያንዳንዱ ሰልጣኝ ስልጠናውን በትኩረት በመከታተል ሰርቲፋይድ (የእውቅና ማረጋገጫ ያገኘ) መሆን ግዴታው ነው። ይህም በዕለት ተዕለት የስራ ተግባራችን ላይ የሚያመጣው ፋይዳ ከፍተኛ ከመሆኑ ባለፈ፣ የራስን ቢዝነስ ለመጀመርና ስራ ፈጣሪ ለመሆን የዲጂታል እውቀት አማራጭ የሌለው መሰረት ነው" ብለዋል።

ይህ የንቅናቄ ሳምንት እስከ ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን፣ በቀጣይ ቀናትም ስልጠናው በስፋት ተደራሽ የሚደረገው በዋናነት፡
በወጣቶች፣
በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፣
በተለያዩ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ላይ ትኩረት በማድረግ ይሆናል።
ይህ ንቅናቄ በደጀን ወረዳና ከተማ አስተዳደር ያለውን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥና የዜጎችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል።

ደጀን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብግንኙነትና ኮሙኑኬሽን

Address

Dejen
Dejen

Telephone

+251587760056

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dejen Polytecnic College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share