Tsedeke Abebaw Asfaw

Tsedeke Abebaw Asfaw tsede

አንድ የመንደር ወጣት ከሱ ሰፈር  የሆነችውን ቁጥብ፣ በጎ እና ሃይማኖተኛ የሆነች ልጅ አገባ። ከተጋቡ ገና አንድ ዓመት እንደሞላቸው ወጣቱ ከአንድ የቅርብ ዘመዱ ጋር ከባድ ግጭት ውስጥ ገባና...
08/07/2025

አንድ የመንደር ወጣት ከሱ ሰፈር የሆነችውን ቁጥብ፣ በጎ እና ሃይማኖተኛ የሆነች ልጅ አገባ። ከተጋቡ ገና አንድ ዓመት እንደሞላቸው ወጣቱ ከአንድ የቅርብ ዘመዱ ጋር ከባድ ግጭት ውስጥ ገባና በከፍተኛ ንዴት ምክንያት ገደለው።

ሰውየውም ከሚስቱ ጋር አካባቢያቸውን ለቆ በመውጣት ራቅ ባለ የገጠር ቀበሌ ውስጥ ከአዲስ ማህበረሰብ ጋር አዲስ ህይወት መኖር ጀመረ።

ወጣቱ የጎጡን ሹም (መሪ) የመሰብሰቢያ ቦታ ያዘወትር ነበር፤ እንደተለመደውም በውይይቶች ይሳተፋል፣ ምክር ይጠይቃል፣ ያወጋ። አንድ ቀን ሹሙ በወጣቱ ቤት አጠገብ ሲያልፍ ቁጥብ፣ ውብና ክብር ያላትን ሚስቱን ለመጀመሪያ ጊዜ አያት።

በዚያች ቅጽበት በሹሙ ልብ ውስጥ ምኞት ተቀጣጠለ። ክፉ አባዜ ተጠናወተውም ባሏን ወደ ጉዞ ልኮ ሚስቱን ብቻዋን በማግኘት ርኩስ ፍላጎቱን ለመፈጸም ክፉ እቅድ አወጣ።

ከጥቂት ቀናት በኋላ በመሰብሰቢያው ቦታ ሹሙ ጉዳዩን አንስቶ እንዲህ አለ፦ "በአንድ አካባቢ በጣም ጥሩ የግጦሽ መሬት እንዳለ ሰምቻለሁ። ጥቂት ሰዎች ሄደው እንዲያዩልኝ እፈልጋለሁ።" ወጣቱንም ጨምሮ አራት ሰዎችን መረጠ። ጉዞው ጥቂት ቀናትን የሚወስድ ነበርና አራቱም ጉዟቸውን ጀመሩ።

በዚያች ሌሊት ሹሙ በድብቅ ወደ ወጣቱ ቤት ሄደ። በጨለማ ውስጥ ግድግዳ ለግድግዳ ሲሄድ ድምጽ ስላሰማ ሚስትየዋ ነቃች። ደንግጣ፣ "ማን ነው?" ስትል ጠየቀች። ሹሙም ማንነቱን ገለጸ።

እሷም፣ "በዚህ ሰዓት? ሁሉ ሰላም ነው?" ስትል ጠየቀች።

ሹሙም የልቡን እንዲህ ሲል ተናገረ፦ "ካየሁሽ ቀን ጀምሮ ልቤ ሰላም አጥቷል። እፈልግሻለሁ፤ የኔ ሁኚ።"

ሴትየዋ በታላቅ ክብር እንዲህ መለሰች፦ "እሺ፣ ይህን በእውነት ከፈለግክ፣ በመጀመሪያ አንድ ጥያቄ መልስልኝ። በትክክል ከመለስክ፣ እንደ ምኞትህ ይሆናል።"

ሹሙ ተደስቶ፣ "ጠይቂ!" አላት።

እሷም አለች፦ "ስጋ እንዳይበላሽ ለመጠበቅ ጨው እንደሚያገለግለው ሁሉ፣ ንገረኝ፣ ጨው ራሱ ቢበላሽ… በምን ይጣፍጣል?" (ወይም ማን ያነጻዋል?)

ሹሙ በጥልቅ ሃሳብ ውስጥ ገባ።

አንድ ሙሉ ቀንና ሌሊት ቢያስብም መልሱን ሊያገኝ አልቻለም።

በማግስቱ በመሰብሰቢያው ቦታ ያንኑ ጥያቄ ለሁሉም አቀረበ፣ ነገር ግን አጥጋቢ መልስ አላገኘም።

አንድ በዕድሜ የገፉ ሽማግሌ ጥግ ላይ በሃሳብ ተውጠው ተቀምጠው ነበር።

ሹሙም፣ "እርስዎ ለምን አይመልሱም?" ሲል ጠየቃቸው።

ሽማግሌውም እንዲህ አሉ፦ "ምክንያቱም ይህ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የጥንት ጥበብ መልዕክት ነውና… ልታዋርድህ፣ ልታሳፍርህ ትችል ነበር፣ ነገር ግን በምትኩ በጥያቄ ህሊናህን ቀሰቀሰች።"

ከዚያም ሽማግሌው ቀጠሉ፦ "ስጋ ሲበላሽ ጨው ይጠብቀዋል። ነገር ግን ጨው ራሱ ከተበላሸ ማን ያድነዋል? ማለትም… ተራው ህዝብ ሲሳሳት እንደ አንተ ያሉ ሹሞች ወደ ጥሩ መንገድ ይመሩታል፤ ነገር ግን ሹሙ ራሱ ከተሳሳተ/ከጠመመ ማን ያስተካክለዋል?"

ይህን ሲሰማ የሹሙ አንገት በሀፍረት ተደፋ፣ አይኖቹም በእንባ ተሞሉ።

እንዲህም አለ፦ "እግዚአብሔር ይጠብቅልኝ። አይኔን ገልጠውልኛል። እግዚአብሔር እንደሚሰውር፣ ስህተቴን ሰውሩልኝ።"

ስጋ በጨው ይድናል፣
ጨው ራሱ ቢበላሽ…
በምን ይድናል?

እኔም እላለሁ፦

አባት ሲሳሳት—ልጆችን ማን ይመራል?

መምህር ሲሳሳት—እውቀትን ማን ያስተምራል?

መሪ ሲሳሳት—ሀገርን ማን ያድናል?

ሁሌም አስታውስ፣ ከጠቢባን ጋር መቀመጥን ተማር።

የሞኞች ስብስብ ልብን ማበላሸት ብቻ ሳይሆን ትውልድንም ያጠፋል።

የ13 ዓመት ልጅ ከመደብር ዳቦ ሲሠርቅ እጅ ከፍንጅ ተያዘ። ከተያዘበት ሊያመልጥ ሲሞክር የመደብሩ መደርደሪያ ወድቆ ተሰበረ።ዳኛው የወንጀሉን ዝርዝር ሰማና ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው!👨‍⚖️"...
08/07/2025

የ13 ዓመት ልጅ ከመደብር ዳቦ ሲሠርቅ እጅ ከፍንጅ ተያዘ። ከተያዘበት ሊያመልጥ ሲሞክር የመደብሩ መደርደሪያ ወድቆ ተሰበረ።
ዳኛው የወንጀሉን ዝርዝር ሰማና ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው!

👨‍⚖️"የሆነ ነገር፥ ማለትም ዳቦ ሰርቀህ ነበር?"

🧑‍🦲ልጁ - (እያፈረ) "አዎን ሰርቄአለሁ"

👨‍⚖️ዳኛው - "ለምን?"

🧑‍🦲ልጁ - "አስፈልጎኝ"

🧑‍⚖ዳኛው - "መግዛት አትችልም ነበር?"

🧑‍🦲ልጁ - "ገንዘብ አልነበረኝም"

🧑‍⚖ዳኛው - "ከቤተሰብህ ለምን አትወስድም?"

🧑‍🦲ልጁ - "እናት ብቻ ናት ያለችኝ፥ እሷም በጠና ታምማ እቤት ተኝታለች"

🧑‍⚖ዳኛው - "ምንም ስራ የለህም?"

🧑‍🦲ልጁ - "መኪና እጥበት እሰራ ነበር፥ ነገር ግን እናቴን ለማስታመም አንድ ቀን ከስራ ስቀር አባረሩኝ"

🧑‍⚖ዳኛው - "ሌሎች እንዲረዱ አልጠየቅኽም?"

🧑‍🦲ልጁ - "በጧት ነው ከቤት የወጣሁ፥ እንዲረዱኝ 50 የሚሆኑ ሰዎች ጋ ሄጄ ነበር፤ አንድም የሚረዳኝ ሰው ግን አላገኘሁም፤ በቃ መጨረሻ ላይ ይህንን መጥፎ ውሳኔ ወሰንሁ"።

ጥያቄው ሲጠናቀቅ #ዳኛው ውሳኔ ማስተላለፍ ጀመረ።

#ውሳኔ🧑‍⚖

"ዳቦ መስረቅ፥ በተለይ የተራበ ልጅ ዳቦ መስረቅ እጅግ በጣም አሳፋሪ ወንጀል ነው፤ እናም እኛ ሁላችንም የዚህ ወንጀል ተጠያቂ ነን። እኔን ጨምሮ በዚህ ቤት ውስጥ ያላችሁ በሙሉ ወንጀለኛና ተጠያቂ ነን። ስለዚህ እያንዳንዱ በዚህ ችሎት ላይ የታደመና እዚህ ቤት ውስጥ ያለ አስር (10) አስር ዶላር$ እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

ማንም ሰው ሳይከፍል መውጣት አይችልም በማለት
👉አስር ዶለር ከኪሱ አውጥቶ ወረቀት ላይ መመዝገብ ጀመረ።
👉በተጨማሪ ዳቦ ቤቱ የተራበ ልጅ ለፖሊስ አሳልፎ በመስጠቱ 1000 ዶላር እንዲከፍል ውሳኔ አስተላለፈ።
👉ይህ በ24 ሰአት ውስጥ ካልተፈጸመ ፍርድ ቤቱ ዳቦ መደብሩን ያሳሽጋል።
👉ፖሊስም የተራበ ልጅ ፍርድ ቤት በማቅረቡ 1000 ዶላር እንዲቀጣለት ወሰነ።
👉የተወሰነለትን ገንዘብ ለልጁ ካስረከበ በኋላ ፍርድ ቤቱ ልጁን ህዝብ ፊት ይቅርታ ጠየቀው!
የዳኛውን ውሳኔ ከሰሙ በኋላ በችሎቱ ላይ የነበሩ ታዳሚዎች ሁሉ በእንባ ተራጩ።
👉የልጁ እጅ ላይ የነበረው ሰንሰለት ተፈታለት። ዳኛው እንባ እየተናነቀው ሲያወራ ልጁ ያይ ነበር።
---------------------------------------
በኛ ማህበረሰብ ውስጥ ያለው የፍትህ ስርዓት ግን ምን ይመስላል? የተራበ ልጅ ዳቦ ሰርቆ ቢያዝ ወንጀሉም እፍረቱም ለህዝቡ ነው ይህ መልዕክት ልብህን ከነካ እባክህን ለአንድ ሰው ዳቦ ግዛ።
👉አንተ እያለ ሌላው ጾም ማደር የለበትም።
👉በዙሪያህ ካሉ ከብዙዎች አንድ መካከል ቢያንስ ለ አንድ ሰው የአቅምህን አድርግ!

!

👉ከብዙዎች ትሻላለህና ካለህ ጥቂት ነገር ላጡት አካፍል!
ይህንን ከባድ ጊዜ ተጋግዘን እንለፈው
ይህንን በማረጋችሁ ፈጣሪ ያስብልናልና!

(Facebook)

01/06/2022
07/02/2022

Hiiiii

20/05/2021

Address

Dire Dawa

Telephone

+251948596196

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tsedeke Abebaw Asfaw posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share