Wolkite Poly Technic College & Satellite Institute

Wolkite Poly Technic College & Satellite Institute Transferring up to date information about training ,technology transfer and industry extension activ

 ።===============================ግንቦት 12/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከኢትዩ-ቴሌኮም በገዛውና ወደ ትግበራ ባስገባው  Educa...
20/05/2026


===============================
ግንቦት 12/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከኢትዩ-ቴሌኮም በገዛውና ወደ ትግበራ ባስገባው Educational Management System (EMS) አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ስልጠና ለአሰልጣኞች መስጠት ጀመረ።

በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ አጅመል መሐመድ እንዳሉት ሲስተሙ በከፍተኛ ወጪ ከኢትዮ-ቴሌኮም የተገዛ እንደሆነና በኮሌጁ ውስጥ እየተተገበረ ለሚገኘው የዲጂታላይዜሽን አሰራር ስርዓትን ለመዘርጋትና ቀልጣፋ የአስተዳደር ስርዓት ለመፍጠር ታስቦ የመጣ መሆኑን አብራርተው፤ ሲስተሙ በአጠቃላይ በኮሌጁ የስልጠና ስርዓት ላይ ከፍተኛ ፋይዳና ሚና ያለው በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ሁሉም በትጋት እንዲሰሩ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

ስልጠና በዋናነት ትኩረት ያደረገው የሲስተሙ አጠቃቀም ለሁሉም አሰልጣኞች ማሳወቅና ማስገንዘብና በቀጣይ አጠቃላይ አሰራራቸው በዚህ ዘመናዊ ሲስተም መሠረት እንዲከውኑ ለማስቻል ያለመ ነው።

በዚህ ስልጠና ላይ ከሁሉም የት/ት ክፍሎች የተውጣጡ አሰልጣኞች የተሳተፉ ሲሆን በቀጣይነት ተደራሽነቱን በማስፋት አሁን የሰለጠኑትን አሰልጣኞች በመጠቀም ለቀሪዎቹ አሰልጣኞች በሙሉ የሚሰጥ ይሆናል።
-----------------------------
!
!
------------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

 !!==============================ግንቦት 12/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከኦርቢት ኢኖቬሽን ኸብ (Orbit Innovation Hub...
20/05/2026

!!
==============================
ግንቦት 12/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከኦርቢት ኢኖቬሽን ኸብ (Orbit Innovation Hub) ጋር በመተባበር ለተመራቂ ሰልጣኞች በስራ ፈጠራ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫና የማነቃቂያ ስልጠና ሰጠ።

የስልጠናው ዋና አላማ ሰልጣኞቹ የኮሌጅ ስልጠናቸውን አጠናቀው እንደወጡ የስራ ፈላጊነት አስተሳሰባቸውን በመቀየር የራሳቸውን ስራ እንዲፈጥሩ ለማድረግ ያለመ ሆኖ በተጨማሪም በኮሌጅ ያገኙትን እውቀትና ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር የስራ ፈጠሪ እንዲሆኑ ለማገዝ፣ የፈጠራ ስራ ሀሳቦቻቸውን ወደ ቢዝነስ የሚቀይሩበትን መንገድ ለማሳየት፣ በዚህ ሂደት ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ተግዳሮቶችን በፅናት የሚያልፉበትን መንገድ ለማሳየት እና በስነ-ልቦና ዝግጁ ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ ነው።

ስልጠናው ልምድና ተሞክሮን በቀጥታ ማጋራት ላይ ያተኮረ ሆኖ በዋናነት ግን በቀላሉ የስራ መፍጠሪያ መንገዶች፣ ከሌሎች ድርጅቶች እና ተቋማት ጋር በአጋርነት በመስራት ምርትና አገልግሎትን በጋራ በጥራትና በስፋት እንዴት ለገበያ ማቅረብ እንደሚቻል እና ጠንካራ የስራ ተነሳሽነትን ስለማሳደግ ላይ ነበር።

ስልጠናውን የወሰዱት በዘንድሮ አመትና ከዚህ በፊት ከኮሌጁ የሚመረቁና ተመርቀው የወጡ ሰልጣኞች ሲሆኑ ስልጠናውን የተሰጡትም ከዚህ በፊት በተመሳሳይ መልኩ ስልጠናዎችን ወስደውና ተግዳሮቶችን አልፈው በተለያዩ የፈጠራ ስራዎች ላይ ተሰማርተው ስኬታማ የሆኑ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች ናቸው።
-----------------------------
!
!
------------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

 ።===================ግንቦት 11/2018 (ወልቂጤ)፡ በወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ህብረተሰብ ተሳትፎ የካምፓሱን ውበት ለመጠበቅና ለስራ እንዲሁም ለመማር ማስተ...
19/05/2026


===================
ግንቦት 11/2018 (ወልቂጤ)፡ በወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ህብረተሰብ ተሳትፎ የካምፓሱን ውበት ለመጠበቅና ለስራ እንዲሁም ለመማር ማስተማር ሂደቱ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ያለመ ታላቅ የፅዳት መርሐ-ግብር ተካሄደ።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የኮሌጁ ዲኖች፣ የአሰልጣኞች፣ የአስ/ሰራተኞች እንዲሁም መላው ሰልጣኞች በአንድነት በመሆን በየምድቡ የፅዳት ስራ አከናውነዋል።

የፅዳት ፕሮግራሙ የአንድ ጊዜ ተግባር ብቻ ሳይሆን መደበኛ የአሰራር ስርዓት ተዘጋጅቶለት በየ15 ቀናቱ በመደበኛነት እየተካሄደ የሚገኝ ነው።

የመርሐ-ግብሩ አላማ የኮሌጁን ግቢ ፅዳት በዘላቂነት ከማስጠበቅ ባሻገር፣ የከይዘን (Kaizen) ትግበራን ቀጣይነት በማጠናከር ባህልን ለማድረግ እንዲሁም ኮሌጁን ማራኪ፣ ሳቢ፣ ውብ በማድረግ ለስራ ምቹ ለማድረግ ታሳቢ ተደርጎ የሚተገበር በመሆኑ በቀጣይም ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።
-----------------------------
!
!
------------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

 ።==============================ግንቦት 07/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ለ11ኛ ዙር የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና ሰጠ። ምዘናውን የ...
15/05/2026


==============================
ግንቦት 07/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ለ11ኛ ዙር የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና ሰጠ። ምዘናውን የወሰዱት ቁጥራቸው 372 የሚሆኑ ስልጠናቸውን በደረጃ ተከታትለው ያጠናቀቁ መደበኛ ሰልጣኞች እና በአጫጭር ጊዜ ስልጠና ወስደው ያጠናቀቁ ለስራ ስምሪት ወደ አረብ ሀገራት ለመሄድ ዜጎች እንዲሁም ከADRA Ethiopia ጋር በመተባበር ለ4ኛ ዙር ስልጠና ወስደው ያጠናቀቁ ሰልጣኞች ናቸው።
------------------------------
!
!
------------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

 ። =============================ግንቦት 05/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ለአስ/ሰራተኞች እና አሠልጣኞች በመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ አ...
13/05/2026


=============================
ግንቦት 05/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ለአስ/ሰራተኞች እና አሠልጣኞች በመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ አሰጣጥና በስራ ቦታ ደህንነት አጠባበቅ ላይ ያተኮረ ስልጠና ሰጠ።

የስልጠናው ዋና አላማ ኮሌጁ እየተገበረ የሚገኘው ISO 21001:2025 (Educational Organizations Management System - EOMS) ውጤታማነት ጥቅም ላይ እንዲውል እንዲሁም በኮሌጁ የሚሰጡ አገልግሎቶች የደንበኞች ፍላጎት ያሟሉና ደህንነቱ የተጠበቀ የስልጠና ከባቢ ለመፍጠር ታሳቢ ያደረገ ነው።
-----------------------------
!
!
-------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

   ።============================ግንቦት 05/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከተስፋ ድርጅት(Hope Enterprise)በማስተር ካርድ ፋ...
13/05/2026


============================
ግንቦት 05/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከተስፋ ድርጅት(Hope Enterprise)በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የSEED ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ከኮሌጁ ጋር አብረው ከሚሰሩ ኢንደስትሪዎች ጋር የኢንደስትሪ ትስስር አውደ-ጥናት አካሄደ።

የአውደ-ጥናቱ ጥናቱ አላማ በኮሌጁና አብረውት ከሚሰሩት ኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን አጋርነት በማጠናከር የክህሎት ልማት ስራው ውጤታማ ለማድረግ እንዲሁም ስልጠና አጠናቃቂ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ነው።

በአውደ ጥናቱ ላይ የሆፕ ኢንተርፕራይዝ አመራሮችና ባለሙያዎች፣ የኮሌጁ ዲኖች፣ የጉራጌ ዞን ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች እና ቴክኒክና ሙያ መምሪያዎች ኃላፊዎች እንዲሁም የትብብር ስልጠና የሚሰጡ ኢንደስትሪዎች ኃላፊዎችና ተወካዮች ተገኝተዋል።

በአውደ-ጥናቱ የተከፈተው በሆፕ ኢንተርፕራይዝ ማኔጀር አቶ ፍሬው ንግግር ሲሆን እሳቸውም እንዳሉት የቴክኒክና ሙያና ኢንዱስትሪ ውጤታማ መሆን የሚችሉት ባላቸው የጠበቀ ትስስር በመሆኑ ሁላችንም ለዚህ መትጋትና መተባበር እንዳለብን አፅንኦት ሰጥተዋል።

በመቀጠል በኢንተርፕራይዙ የተዘጋጀ ለውይይት መነሻ የሚሆን ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል። በውይይቱም በርካታ አስተያየቶች ከተሳታፊዎች የተነሱ ሲሆን ለአብነትም ከኮሌጁ ጋር ጥሩ ግንኙነትና ትብብር እየተፈጠረ መሆኑን፣ ሰልጣኞች ለትብብር ስልጠና ሲወጡ ተገቢ ክትትል መደረግ እንዳለበት፣ በስልጠና ወቅት የግብዓት እጥረት ስላለብን ድጋፍ ቢደረግ፣ መሠል የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች በተከታታይ መደረግ ቢቻል፣ ኢንደስትሪዎች የሰለጠነ የሰው ሀይል በብዛት ስለሚፈልጉ ተቀራርቦ መሠራት ቢቻል የሚሉ ገንቢ ሀሳቦች ተነስተው በግብዓትነት ተወስዷል።

በመጨረሻም አውደ-ጥናቱን የተጠቃለለው በኮሌጁ ዲን አቶ ኸይሩ አህመዲን ሲሆኑ እንዳሉት የሁለታችን ትስስር ለስራችን ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስላለው እንዲጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ፣ ኢንደስትሪዎች የኮሌጁን ሀብት በማንኛውም ጊዜ መጠቀም እንደሚችሉና በጋራ መስራት እንደሚቻል ሁሌም ክፍት መሆኑን በመግለፅ ተጠናቋል።
----------------------------
!
!
-------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

 ።============================ግንቦት 03/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የአሰልጣ...
11/05/2026


============================
ግንቦት 03/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የአሰልጣኞችን የክህሎት ክፍተት መሙላት ያለመ 2ኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

ይህ ስልጠና በዋናነት በተቋም ውስጥ የሚገኙ አሰልጣኞችን እና በኢንዱስትሪ ውስጥ የትብብር ስልጠና (Cooperative Training) የሚሰጡ ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ ሆኖ ከ30 በላይ የሚሆኑ በውሃና በግንባታ ሙያ ዘርፍ የተሰማሩ የኮሌጁ አሰልጣኞች እንዲሁም በአበሽጌ ወረዳና በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የውሃ ጽ/ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የስልጠናው ዋና ትኩረት በውሃና ሳኒቴሪ ዘርፍ በተለይም የውሃ መስመር ዝርጋታ ዲዛይን መስሪያ ሶፍትዌር (Water Supply Network Design Software) አጠቃቀም ላይ ሰፊ ግንዛቤና ተግባራዊ ክህሎት የሚሰጥበት ነው።

የአቅም ግንባታ ስልጠናውን እየተሰጠ የሚገኘው ከኢንስቲትዩቱ በመጡና ከፍተኛ ልምድ ያካበቱት ባለሙያዎች አቶ ዳንኤል ድሪባ እና አቶ ሎሎ አድነው አማካኝነት ነው።

ስልጠናው ከንድፈ-ሀሳብና የተግባር በዘለለ ፕሮጀክት ተኮር (Project-based) በመሆኑ ሲጠቃለል የኮሌጁን የውሃ ማጠራቀሚያ ገንዳ (Water Reservoir Design) ዲዛይን እንዲሰሩ የሚደረግ ይሆናል።

በአጠቃላይ ኮሌጁ መሰል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ለመስጠት ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር የመስራት ሂደቱ አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። በዚሁ አጋጣሚ ስልጠናውን ላዘጋጀልንና ከዚህ በፊትም የተለያዩ ድጋፎችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገልን ለሚገኘው ኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከልብ የመነጨ ምስጋናውን ያቀርባል።
----------------------------
!
!
-------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

05/05/2026

!!
!!
=============================
ሚያዝያ 26/2018 (ወልቂጤ)፡ ​የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር በተከታታይ ተመራቂ ሰልጣኞቻችን በመመልመልና የስራ ማስጀመሪያ ስልጠና በመስጠት ከስራ ጋር በማስተሳሰር ጥሩ እድል መፍጠር ችሏል። በመሆኑም አሁን ደግሞ ለተጨማሪ ሰልጣኞች ስልጠና ሰጥቶ ወደ ስራ ለማሰማራት ፕሮግራም ስለያዘ ከዚህ በፊት ስልጠና ያልወሰዳችሁ ሰልጣኞች በሙሉ እስከ ሚያዝያ 28/2018 ዓ.ም በኮሌጁ የሰው ሃይል ልማትና ተቋም አቅም ግንባታ ዋና የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 19 መጥታችሁ እንድትመዘገቡና ከሚያዝያ 29/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ደግሞ ስልጠናው የሚጀመር በመሆኑ በኮሌጁ ተገኝታችሁ ስልጠናውን እንድትጀምሩና የዚህ መልካም እድል ተጠቃሚ እንድትሆኑ ስንል ጥሪያችንን በአክብሮት እናስተላልፋለን፡፡
#ኮሌጁ!!

 !! ።=============================ሚያዝያ 26/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ለዘርፈ-ብዙ ተግባራቶቹ አገልግሎት ሊውል የሚችል የጥልቅ...
04/05/2026

!!

=============================
ሚያዝያ 26/2018 (ወልቂጤ)፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ለዘርፈ-ብዙ ተግባራቶቹ አገልግሎት ሊውል የሚችል የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ስራ ፕሮጀክት አስጀመረ።

ፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም በአካባቢው በተለይም በበጋ ወቅቶች ይገጥም የነበረው የውሃ እጥረት በዘላቂነት እንዲፈታ ታሳቢ ተደርጎ በ3.2 ሚሊዮን ብር ወጪ በዘርፉ ልምድና ባለው ኮንትራክተር አማካኝነት በፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።

በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለአብነት ለኮሌጁ ማህበረሰብ አስተማማኝ የውሃ አቅርቦት ለማድረግ፣ በሙያው ስልጠና ዘርፍ የተግባር ሥልጠናን በአግባቡ ለመስጠት፣ ኮሌጁን ግቢ ውብና ማራኪ ለማድረግ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን በስፋት ለመስራት፣ በግቢ ውስጥ በመስኖ ስራ የአትክልትና ፍራፍሬን በስፋት በማምረት የውስጥ ገቢን ለማሳደግ፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ የንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሁም ለሌሎችም ዘርፈ-ብዙ አገልግሎቶችን ለማከናወን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
----------------------------
!
!
-------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

 ።==============================ሚያዝያ 22/2018 (ወልቂጤ)፡ ADRA Ethiopia ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ኮሚ...
01/05/2026


==============================
ሚያዝያ 22/2018 (ወልቂጤ)፡ ADRA Ethiopia ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን (EECMY-DASSC) ጋር በመተባበር በወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓሶች የሚተገበረው የGreen Energy Project ስር እስካሁን ያከናወናቸው ተግባራት ላይ ትኩረት ያደረገ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ።

በጉብኝቱ ላይ ከADRA Ethiopia ዋናው መስሪያ ቤት የመጡ እንግዶች፣ የፕሮጀክቱ የስቲሪንግ ኮሚቴ አባላት፣ የኮሌጁ ዲን እንዲሁም በፕሮጀክቱ የኮሌጁ አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል።

በጉብኝቱ ምልከታ የተደረገባቸው በፕሮጀክቱ ድጋፍ በሶላር ሙያ ስልጠና በኮሌጁ ወስደው ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡና የመሳሪያ ድጋፍ ያገኙ በጉራጌ ዞን በአበሽጌ ወረዳ (ቁሊት) የሶላርና የኤሌክትሪክ ዝርጋታና ጥገና ማህበር በሶላር ሃይል የሚሰራ ወፍጮ በመትከል ለአካባቢው ማህበረሰብ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ፤ በቸሃ ወረዳ የሶላር ቴክኖሎጂን በመጠቀም በዘመናዊ የመስኖ ስራ (Irrigation) ተሰማርተው እየሰሩ የሚገኙ እንዲሁም በወልቂጤ ከተማ በሶላር የሚሰራ የዘይት መጭመቂያ ማሽን እና ስቶቭ (Stove) በመጠቀም የዘይት ምርት፣ የቺፕስ፣ የሳምቡሳና የእርጥብ ስራዎችን እየሰሩ ውጤታማ የሆኑ ማህበራት ናቸው።

በጉብኝቱ የተሳተፉ እንግዶችና ባለድርሻ አካላት እንዳሉት ፕሮጀክቱ በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራና በአካባቢ ጥበቃ ላይ እያመጣ ያለው ለውጥ የሚበረታታ በመሆኑ በቀጣይ ተደራጅተው ወደ ስራ ለገቡና በሂደት ላይ ለሚገኙ ማህበራት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ አረጋግጠው በፕሮጀክቱ የመጡ ተጨባጭ ውጤቶች እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን በመግለፅ ለስኬታማነቱ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
----------------------------
!
!
-------------------------

Facebook፡- https://www.facebook.com/wolkite poly technic college & satellite institute
Website:- https://wptc.gov.et/
Telegram:- https://t.me/wptc2000
!

 ።========================ሚያዝያ 21/2018 (ወልቂጤ)፡ ADRA Ethiopia ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማት ቢሮ (EECMY-DASSC) ጋር በመ...
29/04/2026


========================
ሚያዝያ 21/2018 (ወልቂጤ)፡ ADRA Ethiopia ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማት ቢሮ (EECMY-DASSC) ጋር በመተባበር በወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ሲተገበር የነበረው የGreen Energy Project ማጠቃለያ የግምገማ መድረክ በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ ከክልል፣ ከዞንና ከከተማ አስተዳደር የተለያዩ የሥራ ዘርፎች የመጡ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት፣ የADRA Ethiopia ዋና ማስተባበሪያ የመጡ አካላት፣ የፕሮጀክቱ የስቲሪንግ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም የኮሌጁ ዲኖች ተገኝተዋል።

መድረኩ የተጀመረው በኮሌጁ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ በአቶ ኤፍሬም ደመቀ አማካኝነት በቀረበ ዝርዝር የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ሲሆን በሪፖርታቸውም ፕሮጀክቱ ከፈረንጆቹ 2023 ጀምሮ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየና በሶላር ኢነርጂ ተከላና ጥገና ዘርፍ ትኩረት አድርጎ በመስራት በ4 ዙሮች 135 ሰልጣኞችን አሰልጥኖ ማብቃት መቻሉን፣ ከስልጠና ባለፈም አደራጅቶና ወደ ሥራ እንዲሰማሩ ለሥራ ማስጀመሪያ የሚሆናቸውን ቁሳቁሶች ድጋፎችን ማድረግ መቻሉንና ፕሮጀክቱ ውጤታማነት ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ የሥራ ግንኙነት መደረጉ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ አብራርተዋል።

ከሪፖርቱ በመቀጠል ፕሮጀክቱ በኮሌጁ ያከናወናቸው ተግባራትን የመጎብኘት መርሃ-ግብር የተካሄደ ሲሆን በጉብኝቱም ወቅትም በ4ኛው ዙር ስልጠና ወስደው ካጠናቀቁ ወጣቶች ጋር ውይይት የማድረግና ተደራጅተው ወደ ስራ ለመግባት ለተዘጋጁ 3 ማህበራት የሥራ ማስጀመሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።

በመጨረሻ የማጠቃለያ የጋራ ውይይት የተካሄደ ሲሆን የውይይቱ ተሳታፊዎች ገንቢ አስተያየቶች ያነሱ ሲሆን በዋናነት ፕሮጀክቱ ከሌሎች መሰል ፕሮጀክቶች በተሻለ ውጤታማና መሬት የነካ በመሆኑ የሚቀጥልበት ሁኔታ መመቻቸት እንዳለበት፤ በቀጣይ የፕሮጀክቱ ድጋፍ በሶላር ኢነርጂ ብቻ ሳይወሰን በሌሎች የሙያ ዘርፎች ላይ ማስፋት እንደሚገባ፣ ባለድርሻ አካላትም ሰልጣኞቹ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሁሉም በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ እና ለፕሮጀክቱ ስኬት የኮሌጁ ማኔጅመንትና የስቲሪንግ ኮሚቴው አባላት ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና ቀርቧል።

የዕለቱ የክብር እንግዳም የውይይት መድረኩን ሲያጠቃልሉ ፕሮጀክቱ ካሳየው አመርቂ ውጤት አንጻር ከአቻ ፕሮጀክቶች የተሻለ መሆኑን ማረጋገጣቸውንና ለቀጣይነቱ ደግሞ የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተውና የቀጣይ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ በስኬት ተጠናቋል።

Address

Near To Wolkite Stadium
Welk'it'e

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251113301590

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolkite Poly Technic College & Satellite Institute posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to Wolkite Poly Technic College & Satellite Institute:

Share