Arba minch chamo compas sosa department students FB group

  • Home
  • Kenya
  • Gilgil
  • Arba minch chamo compas sosa department students FB group

Arba minch chamo compas sosa department students FB group sociology is back bone of society "

24/03/2026

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነገ በዋናው ግቢ በሚገኘው የምረቃ አዳራሽ ደማቅ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ያካሂዳል። ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መርሐ ግብሮች ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ድረስ ያሰለጠናቸውን ዕጩ ተመራቂዎች ለምርቃት ያበቃል።

ወድ ተመራቂዎቻችን ለዓመታት በለፋችሁበት የትምህርት ዘርፍ ለዚህ ክብር በመብቃታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ! ነገ የምትቀበሉት ዲግሪ የድካማችሁ ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ ለሀገራችን ብሩህ ተስፋና ዕውቀት የምታበረክቱበት አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ ነው። የወደፊት ጉዟችሁ የጥበብና የውጤት ይሁንላችሁ!

እንኳን ደስ ያላችሁ!

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ

የጥበብ ምንጭ/Spring of Wisdom

Arba Minch University will host a grand graduation ceremony tomorrow at the Graduation Hall located on the Main Campus. The university is proud to graduate candidates who have completed their studies across various programs, ranging from Undergraduate degrees to PhDs.

To Our Dear Graduates: Congratulations on reaching this prestigious milestone through years of hard work in your respective fields! The degree you receive tomorrow is not only the fruit of your labor but also the beginning of a new chapter where you will contribute knowledge and hope to our country's bright future.

May your future journey be filled with wisdom and success! Congratulations once again!

Arba Minch University "Spring of Wisdom"

ለአምዩ ተማሪዎች (UG, PG and PhD) በሙሉየኤሌክትሮኒክ ትምህርትን (e-Learning) በተመለከተ በተለያዩ ጊዜያት የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች መካሄዳቸው ይታወሳል።በዚህም መሠረት ...
25/12/2025

ለአምዩ ተማሪዎች (UG, PG and PhD) በሙሉ

የኤሌክትሮኒክ ትምህርትን (e-Learning) በተመለከተ በተለያዩ ጊዜያት የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች መካሄዳቸው ይታወሳል።

በዚህም መሠረት ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በትንሹ 7 የSSS ሥልጠናዎችን በመውሰድ ማጠናቀቅ ያለባቸው ሲሆን ማንኛውም ተማሪ የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት (Second Semester) ምዝገባ ለማካሄድ ሥልጠናውን መውሰድ ስላለበት ከወዲሁ አስፈላጊውን ሁሉ እንድታደርጉ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ፡- የ5 million Coders ሥልጠናዎችን (በትንሹ 1) ማጠናቀቅ ያስፈልጋል።

ለተጨማሪ መረጃ የካምፓስ ኤሌክትሮኒክ ት/ክፍል አስተባባሪዎችን ያናግሩ።

የአምዩ ኤሌክትሮኒክ ት/ክፍል አስተዳደር

Amu
04/09/2025

Amu

የተማሪዎች የመግቢያ ጥሪ ማስታወቂያ

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነባር እና አዲስ ገቢ ተማሪዎች በሙሉ፤

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነባር የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ እና ኢ-መደበኛ መርሃ-ግብር ተማሪዎች የ2018 ትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ እሁድ መስከረም 4 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ምዝገባ ሰኞ እና ማክሰኞ መስከረም 5 እና 6 ቀን 2018 ዓ.ም፣ እና ትምህርት መጀመሪያ ረቡዕ መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-

የ2018 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ አመት (አዲስ) ተማሪዎች፣ እንዲሁም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2017 የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ያጠናቀቁና የትምህርት ሚኒስቴር የማለፊያ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች መግቢያ ከትምህርት ሚኒስቴር የአዲስ ገቢ ተማሪዎች መረጃ እንደደረሰን ወድያውኑ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡

በ2017 ትምህርት ዘመን 1ኛ ዓመት ትምህርት አጠናቀው ትምህርት ክፍል ምደባ ያላገኙ ተማሪዎች ትምህርት ክፍል ምርጫ ሰኞ መስከረም 05 ቀን 2018 ዓ.ም.፣ ምደባ የሚፈጸመው ማክሰኞ መስከረም 06 ቀን 2018 ዓ.ም.፣ ውጤት የሚገለጸው ረቡዕ መስከረም 07 ቀን 2017 ዓ.ም. ይሆናል፡፡

ሁሉም የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች ከምዝገባ በፊት በኤሌክትሮኒክ ትምህርት አስተዳደር ክፍል አስተባባሪነት የሚሰጠውን የ e-SHE SSS ሥልጠና በማጠናቀቅ ቢያንስ አንድ (1) ሰርተፊኬት ማግኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡

ከላይ ከተጠቀሱት ቀናት ቀድመውም ሆነ ዘግይተው የሚመጡ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እናሳስባለን፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

Address

Secha,sub City
Gilgil

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arba minch chamo compas sosa department students FB group posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share