Bonga University

Bonga University Bonga University is one of the Public Higher Educational Institution in Ethiopia.
(1)

‎ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለማህበረሰብ ሬድዮ  ሰራተኞች ስልጠና ሰጠ።‎‎።።።።።።።ሰኔ 1/2018 ዓ.ም።።።።።።።‎‎ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረስብ ሬድዮ ጣቢያ FM-92.1ላይ በፈቃደኝ...
08/06/2026

‎ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለማህበረሰብ ሬድዮ ሰራተኞች ስልጠና ሰጠ።

‎።።።።።።።ሰኔ 1/2018 ዓ.ም።።።።።።።

‎ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረስብ ሬድዮ ጣቢያ FM-92.1ላይ በፈቃደኝነት እያገለገሉ ላሉ እና ፊላጎት ላላቸው መምህራን ፣ የአስተዳደር ስራተኞችና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል።

በመድረኩ ተገኝተው ‎የመክፈቻ ነግግር ያደረጉት የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ መማ/ማስ/ምር/ማህ/አገ/ቴክ/ስር/ም/ኘሬዝዳንት ከለለው አዲሱ (ዶ/ር) ናቸው።

ምክትል ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው በግልጽ እንዳሰፈሩት ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማረጋገጥ የራሱን የሬድዮ ጣቢያ መክፈቱን ገልጸዋል።

በመሆኑም ‎የሬድዮ ጣቢያ ማቋቋም ብቻ ሳይሆን የሰው ሀይል ልማት ላይ መስራት እንዲሁም ማፊራት አስፈላጊ እንደሆነ ገልፀዋል።

የዛሬውም ስልጠና የዚሁ አካል በመሆኑ ሙያው በሚፈልገው ልክ ሰራተኞችን ለማብቃት የታለመ እንደሆነ አስገንዝበዋል።

‎በተጨማሪም ሚዲያ የተቋምን ገጽታ ለመገንባት ወሳኝ በመሆኑ በሙያው የታነፀ ባለሙያ ሲኖር ደግሞ ጣቢያው የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን አብራርተዋል።

ሰልጣኞችም ስልጠናውን በሀላፊነት ስሜት በመከታተል የሬድዮ ጣቢያውን ወደተሻለ ከፍታ በማሸጋገር ለተቋማዊ ለውጥ የበኩላችሁን እንድትወጡ በማለት በይፋ ስልጠናውን አስጀምረዋል።

‎ስልጠናውን ከደቡብ ሬድዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ቦንጋ ቅርንጫፍ የመጡ ባለሙያዎች በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ሰጥተዋል።

‎በተጨማሪም ከመሠረታዊ ጽንሰ-ሀሳብ ባሻገር ‎በተግባር የተደገፈ ስልጠናም የመርሀ-ግብሩ አካል ነበር።

የዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ በዋናነት ስልጠናውን አስተባብሯል።

‌‎በጋራ እንችላለን!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከካፋ ዞን የተለያዩ ወረዳ እና ከተማ አስ/ር  ለተወጣጡ የተፈጥሮ ሀብት አያያዝ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ።         ግንቦት 28/2018 ዓ.ምስልጠናው በዋናነት በGeo s...
05/06/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከካፋ ዞን የተለያዩ ወረዳ እና ከተማ አስ/ር ለተወጣጡ የተፈጥሮ ሀብት አያያዝ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ።

ግንቦት 28/2018 ዓ.ም

ስልጠናው በዋናነት በGeo spatial Software skill ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አሰተባባሪነት ነበር የተሰጠው።

በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ከለለው አዲሱ (ዶ/ር) የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ መማ/ማስ/ምር/ቴክ/ሽግ/ማህ/ጉድ /ም/ፕሬዝዳንት ሰልጣኞችን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን. . .

አክለውም ም/ፕሬዝዳንቱ እንደገለፁት ያለንን የተፈጥሮ ሀብት ለማስተዳደር እና መጠቀም የሚያስችል ስልጠና እንደሆነ ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም በተፈጥሮ ሀብት ለታደለው ለእንደኛ አይነት አካባቢ የGeo spatial siftware Skill ስልጠና ፋይዳው የጎላ እንደሆነ አሳስበው ሰልጣኞች በትኩረት እንዲከታተሉ አስገንዝበዋል።

ስልጠናውን የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የጂኦግራፊ ት/ት ክፍል መምህርና የብዝሀ ህይወት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ጊንጆ ጊትማ (ዶ/ር) ከሌሎች የት/ት ክፍሉ GIS and Remote Sensing እንዲሁም የደን ሀብት ጥበቃ /Forestry/ ምሁራን ጋር በመሆን ሰጥተዋል።

በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የግብርናና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጽ/ቤት ባለሙያዎች በበኩላቸው በስልጠናው መሠረታዊ የሆኑ የክህሎት ክፍተቶቻችንን መሙላት ችለናል ብለዋል።

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲም እንደዚህ አይነት ስልጠና ማዘጋጀቱ ተቋሙን ለየት ያደርገዋል በማለት ለዩኒቨርሲቲው ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።

በጋራ እንችላለን!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ሀገር ዓቀፍ የአቅም ማሻሻያ /Remedial/ተማሪዎች ፈተና መስጠት ተጀመረ።       *ግንቦት 27/2018ዓ.ም*ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ሀገር ዓቀፉን የአቅም ማሻሻ...
04/06/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ሀገር ዓቀፍ የአቅም ማሻሻያ /Remedial/ተማሪዎች ፈተና መስጠት ተጀመረ።

*ግንቦት 27/2018ዓ.ም*

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ሀገር ዓቀፉን የአቅም ማሻሻያ /Remedial /ተማሪዎች ፈተና መስጠት ጀምሯል።

ፈተናው በበይነ - መረብ /Online / እንደመሰጠቱ ተማሪዎች ተገቢው የፀጥታ ስርዓቶችን እንዲፈፅሙ በማድረግ ወደመፈተኛ ክፍል ገብተዋል።

ፈተናው ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ስድስት ቀናት ይሰጣል።

በዚህ ጊዜም ተማሪዎች ተገቢውን የፈተና ስነ-ሥርዓት በመከተል ፈተናውን ተረጋግተው በመስራት ተገቢውን እንዲፈፅሙ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ያሳስባል።

በጋራ እንችላለን!

የአቅም ማሻሻያ /Remedial/ ፈተናን አስመልክቶ  ለተለያዩ አካላት ገለፃ ተደረገ።             *ግንቦት 26/2018 ዓ.ም*የ2018 ዓ.ም ሀገር ዓቀፍ የአቅም ማሻሻያ /Remedi...
03/06/2026

የአቅም ማሻሻያ /Remedial/ ፈተናን አስመልክቶ ለተለያዩ አካላት ገለፃ ተደረገ።

*ግንቦት 26/2018 ዓ.ም*

የ2018 ዓ.ም ሀገር ዓቀፍ የአቅም ማሻሻያ /Remedial/ ፈተና አስመልክቶ ለቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አስፈፃሚ አካላት ገለፃ ተደረገ።

በዩኒቨርሲቲው የመማ/ ማስ/ ምር/ ማ/ አገ/ እና ቴክ/ስር/ም/ፕሬዝዳንት ከለለው አዲሱ(ዶ/ር) መሪነት ነበር መድረኩ የተካሄደው።

በተጨማሪም ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ት/ት ሚ/ር ፈተናውን ለማስተባበር የመጡት አቶ ተክል ዘለቀ ባደረጉት ገለፃ ለሁሉም ፈፃሚ አካላት ተግባር እና ሀላፊነት ዙሪያ ገለፃ ሰጥተዋል።

ፈተናው እንደተለመደው በበይነ መረብ /Online /እንደመሆኑ ተገቢውን በማድረግ የተሳካ የፈተና ሂደት ማከናወን የሁሉም ሀላፊነት ሊሆን እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

በመጨረሻም ከለለው አዲሱ (ዶ/ር)በሠጡት ማጠቃለያ ይሄንን ትልቅ ሀገራዊ ሀላፊነት በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን ሁላችንም የበኩላችንን መተግበር ይገባናል በማለት የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ተማሪዎችም ፈተናውን በአገባቡ ከመፈተን አንፃር የተለመዱ የፈተና ሥነ-ሰርዓቶችን በመጠበቅ ግዴታችሁን እንድትወጡ በማለት ዩኒቨርሲቲው መልእክት ያስተላልፋል።

ፈተናው ከግንቦት 27 - ሰኔ 03/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀ-ግብር መረዳት ይቻላል።

በጋራ እንቸላለን!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአካዳሚክ ፕሮግራም ዕውቅና ያዘጋጀውን ሰነድ (Academic Program Accreditation Documents )  አስገመገመ::            **ግንቦት 22/2018 ...
01/06/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአካዳሚክ ፕሮግራም ዕውቅና ያዘጋጀውን ሰነድ (Academic Program Accreditation Documents ) አስገመገመ::

**ግንቦት 22/2018 ዓ.ም*

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው የአዳዳሚክ ፕሮግራም ሰነድ ግምገማ ተገኝተው ሙያዊ ድጋፍ እና ግምገማውን ያከናወኑት የኢትዮጵያ ት/ት እና ስልጠና ባለስልጣን /ETA/ ከፍተኛ ባለሙያዎች ናቸው።

በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦንጋ ዩኒቨርሰቲ ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር)ናቸው።

ክቡር ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ለዩኒቨርስቲው ከተሰጡት ቁልፍ ተግባራት (KPI's) መካከል አንዱ የዩኒቨርቲው ትኩረት መስክ ልየታ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

ይህንኑ መሠረት በማድረግ ከተለዩ አካዳሚክ ፕሮግራሞች መካከል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለሚያስተምራቸው 25 የመጀመሪያ ድግሪ ፕሮግራሞችን ሦስቱን ዕውቅና የማሰጠት ተግባር መሆኑን አውስተው ለዚህም በትኩረት ሲሠራበት ቆይቷል ብለዋል።

የመማር ማስ/ምር/ማህ/አገ/ቴክ/ሽግ/ም/ፕሬዝዳንት ከለለው አዲሱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተማሪ ተቀብለን የምናስተምርባቸው ሁሉም አካዳሚክ ፕሮግራሞች ዕውቅና ያላቸውና የሚጠበቅባቸውን አገራዊ ልኬት የሚያሟሉ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል።

በመሆኑም በተሰጠን KPI መሠረት አካዳሚክ ፕሮግራሞቻችን ዕውቅና ያላቸው እንዲሆኑ ለሁሉም ትምህርት ክፍል መምህራን ስለአካዳሚክ ፕሮግራም ዕውቅና (Academic Program Accreditation) ፋይዳ፣ ጥቅም እና አሠራር ዙርያ ተገቢው ሥልጠና ተሠጥቷል ብለዋል።

በመሆኑም ሥራውን በባለቤትነት የሚሠሩ አካላትን በሁሉም ትምህርት ክፍሎች ተሰይሟል።

በዚሁ መሠረት የውስጥ ግምገማ (Internal Validation) ውጤት መሠረት በማድረግ የተሻለ የሰነድ ዝግጅት ደረጃ ላይ የሚገኙትን አራት ፕሮግራሞች መለየት ተችሏል::

ለመጥቀስ ያህል:-

1. የተፈጥሮ ሀብት አጠባበቅ ትምህርት ክፍል
2. የአፈር እና ውሃ ሀብት አያያዝ ትምህርት ክፍል
3. የግብርና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል እና
4. የምጣኔ ሀብት /Economics/ ትምህርት ክፍል ናቸው።

የተዘጋጀው ሰነድም ከETA ለመጡ ባለሙያዎች ለAccreditation Documents Validation Team ቀርቦ ወደ ቀጣዩ ደረጃ በሚሻገርበት ሁኔታ ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ባስተላለፉት መልዕክት ለዚህ ትልቅ ተግባር ስኬት አበርክቶ ለነበራቸው አካላት ለETA ባለሙያዎች ጭምር ምስጋናቸውን ችረዋል።

በጋራ እንችላለን!!

Bonga University has officially launched a National Academic Program Standard Development Workshop.           *May 29, 2...
29/05/2026

Bonga University has officially launched a National Academic Program Standard Development Workshop.

*May 29, 2026**

The workshop was launched in collaboration with the Ethiopian Training Authority (ETA).

The academic standard development workshop primarily focuses on two of Bonga University’s flagship programs: Coffee Science and Technology and the Kafi Noonoo Language.

In his opening remarks, Dr. Degela Ergeno clearly emphasized that, developing national standards for these unique academic programs is a vital step toward enhancing educational quality and ensuring compliance with national accreditation benchmarks.

Beyond benefiting Bonga University, these newly established standards will serve as a valuable blueprint for other academic institutions ; asserted by the ETA deligates.

Together, We Can!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ "Research Theme and  Ethics"  /የምርምር ጭብጥ እና  ስነ-ምግባር / በሚል መሪ ቃል ለመምህራን ስልጠና እየሠጠ ይገኛል።        ****** ግንቦት 20...
28/05/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ "Research Theme and Ethics" /የምርምር ጭብጥ እና ስነ-ምግባር / በሚል መሪ ቃል ለመምህራን ስልጠና እየሠጠ ይገኛል።

****** ግንቦት 20/2018 ዓ.ም*******

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የመምህራንን የምርምር አጻጻፍ ብቃት እና አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ሲሆን ይህም ስልጠና የዚሁ አካል መሆኑ ተጠቁሟል።

​መድረኩን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) ሲሆኑ፣ ክቡር ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው እንደገለፁት የመምህራን አቅም ግንባታ ላይ መስራት ለመምህሩም ሆነ ለተቋሙ ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑን አስገንዝበዋል።

አክለውም ክፍተቶች ባሉባቸው ቦታዎች ላይ ተለይተው ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ጠቁመው ስልጠናውን ለመስጠት ከት/ት ሚኒሴቴር የመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎችን አመስግነዋል።

ስልጠናው የትምህርት ሚኒስቴርን የምርምርና ቴክኖሎጂ ማሻሻያ /Reform/ ይዘት ግንዛቤ ማስጨበጥ መሠረት ያደረገ ነው።

ሀገራዊ የምርምር ይዘትን ተከትሎ መስራት እና የምርምር መሰረታዊ ምክንያት ማህበረሰባዊ ለውጥና ውጤታማ መሆን እንደሚገባም ተገልጿል።

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ት/ት ሚ/ር የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት ዋና ስራ አስፈፃሚ ሰራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) የበይነ - መረብ /Online/ስልጠናው ከሌሎች ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር እየሰጡ ይገኛሉ።

ስልጠናው ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲቀጥል በቀጣይ ቀን ደግሞ በከፍተኛ ተመራማሪ ምሁር አንዷለም አየለ (ዶ/ር) እና ባልደረቦቻቸው አማካኝነት ስልጠናው እንደሚሰጥ ከወጣው መርሀ -ግብር መረዳት ይቻላል።

በጋራ እንችላለን!

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎች የአረፋ በዓልን በደማቅ ሁኔታ አከበሩ።          **ግንቦት 19/2018 ዓ.ም*የ1447ኛው የኢድ -አድሃ /አረፋ / በዓል የቦንጋ...
27/05/2026

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎች የአረፋ በዓልን በደማቅ ሁኔታ አከበሩ።

**ግንቦት 19/2018 ዓ.ም*

የ1447ኛው የኢድ -አድሃ /አረፋ / በዓል የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል።

የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች የተከበሩ አቶ ተረፈ ሀ/ማሪያም እንዲሁም መ/ር አበራ ሀይሌ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ሀላፊ እና የተማሪዎች ዲን ተገኝተዋል።

ከፍተኛ አመራሮቹ በየተራ ባሰሙት መልዕክት ተማሪዎችን እና መላ የእምነቱ ተከታዮችን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በተጨማሪም ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ርቀው እንደማክበራቸው ዩኒቨርሲቲው እናንተን ለማስደሰት የሚችለውን ሁሉ አድርጓል ብለዋል።

ተማሪዎችም ዩኒቨርሲቲው እንደቤተሰብ ሆኖ ላደረገላቸው ልዩ የበዓል ዝግጅት ምስጋናቸውን ገልጸዋል።

በተማሪዎች የተዘጋጁ መንፈሳዊ እና ሌሎች ዝግጅቶችም የበዓሉ ድምቀቶች ነበሩ።

ዒድ -ሙባረክ!

በጋራ እንችላለን!

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ የበዓል  መልካም ምኞት  መልዕክታቸውን  አስተላለፉ።          **ግንቦት 18/2018 ዓ.ም*የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ...
26/05/2026

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ የበዓል መልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላለፉ።

**ግንቦት 18/2018 ዓ.ም*

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) ለመላው የዩኒቨርሲቲያችን እና ኢትዮጵያውን የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ክቡር ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው እንደገለፁት እንኳን ለ1447ኛ የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።

በዓሉን ስናከብር የተለመደ የመረዳዳት ባህላችንን በማሰብ ካለን ለተቸገሩ በማካፈል ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።

በመጨረሻም በዓሉ የሰላም ፣ የጤና እና የደስታ እንዲሆን ምኞታቸውን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በማስተላለፍ መልዕክታቸውን ቋጭተዋል።

ዒድ ሙባረክ!

በጋራ እንችላለን!

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የችግኝ ሽያጭ እና ተቋማዊ አሰራር ሁኔታዎች።         ግንቦት 17/2018 ዓ.ም**ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ  ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ከመንግስት የተሰጡትን የመማር ማስተማር ...
25/05/2026

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የችግኝ ሽያጭ እና ተቋማዊ አሰራር ሁኔታዎች።

ግንቦት 17/2018 ዓ.ም**

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ከመንግስት የተሰጡትን የመማር ማስተማር ፣ ምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ተግባራት በአግባቡ እየከወነ ይገኛል።

በዚህም እስካሁን በተጓዘባቸው መንገዶች ሁሉ ከመማር ማስተማር እና ምርምር ተግባራቱ በተጓዳኝ ለህብረተሰቡ በሚሰጣቸው ሁለንተናዊ አገልግሎት አንቱታን ከማትረፍ አልፎ የሕዝብ ወገንተኝነቱን አሳይቷል።

ዩኒቨርሲቲው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከራሱ አልፎ ለህብረተሰቡ በምርምር የለሙ በርካታ ችግኞችን ሲያስተላልፍ ቆይቷል እያስተላለፈም ይገኛል።

ለአብነትም ባለፈው ዓመት በ2017ዓ.ም ክረምት ወቅት በርካታ የቡና ችግኞችን አማራ ክልል መሸጣችን ይታወቃል።

ይህንን ስናደርግ በግቢያችን ባሉ ሰፊ ሄክታር መሬት የአናናስ መትከያ ስፍራዎች ተዘጋጅተው የተረፉ ችግኞች መሆናቸውንም ለመግለጽ እንወዳለን።

በዚሁ መሠረት የሽያጭ ማስታወቂያችንም ቢሆን ግልፀኝነትን በተከተለ እና በማህበራዊ ሚዲያ ገፁም፣ በማህበረሰብ ሬድዮ ጣብያውም ኤፍ .ኤም 92.1 በማሳወቅ ነው።

በቅርቡም ለማህበረሰብ አገልግሎት እና ለሽያጭ ያለማናቸውን የቡና ፣ የአናናስ ፣ የሮዝመሪ/ጥብስ ቅጠል/ የብርቱኳን ፣ የአቮካዶ ችግኝ ሽያጭ ማስታወቂያ ስናስነግር ግልጽ የሆኑ አካሄዶችን ተከትለናል።

የችግኝ ሽያጮቹን ማስታወቂያ ስናወጣም ቅድሚያ ለማህበረሰባችን በመስጠት ነው። ይህንንም ስናደርግ በስጦታ እና በተመጣጣኝ ዋጋ ሽያጭ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ ዩኒቨርሲቲያችን የተደራሽነት አድማሱን በማስፋት ተቋማዊ የሆነ አሰራርን በተከተለ መልኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ የአናናስ ችግኝ ሽያጭ ጥያቄ አቅርቦልናል።

ይህም የግዥ ጥያቄ የመንግስት የፋይናንስ አሰራርን በተከተለ መልኩ ተፈጽሟል።

ነገር ግን ይህንን ተግባር በበጎ ህሊና ባለማየት ወዳልተፈለገ አቅጣጫ በመውሰድ ህብረተሰባችንን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሚለቀቅ አሉባልታ፣ መሠረተ ቢስና እውነትነት የጎደለው መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

አሁንም ቢሆን የአናናስም ሆነ ሌሎች ችግኞችን መግዛት የሚፈለግ የትኛውም የህብረተሰብ ክፍል በማስታወቂያው መሠረት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንደምትችሉ ማሳወቅ አንወዳለን።

በጋራ እንችላለን!

Address

Bonga
334

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bonga University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share