10/09/2026
የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የአዲስ ዓመት መልካም ምኞታቸውን ገለፁ።
:::::::::::::::::::ጳጉሜ 05/2019 ዓ.ም:::::::::::::::::
የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) ለመላው የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ እንዲሁም ለኢትዮጵያውያን በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ክቡር ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው መላው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ብለዋል።
በተለይ የዘንድሮው 2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት ለኛ ለኢትዮጵያውያን በብዙ መልኩ የተለየ መሆኑን ገልፀዋል።
ለዚህም ማሳያው ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ እና የሀገራዊ ምክክርን ባሳካንበት ማግስት መሆኑ አዲሱን ዓመት የተለየ ያደርገዋል።
ይሄም የዴሞክራሲ ባህላችንና እኛ ኢትዮጵያውን ምን ያህል ቁጭ ብሎ የመነጋገር የቆየ ባህል እንዳለን ማሳያ እንደሆነ በአድናቆት ገልፀዋል።
መጪው አዲስ ዓመትም እንደ ዩኒቨርሲቲም እንደ ሀገርም የጀመርናቸውን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን የምናሳካበት እና የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ እድገት የበለጠ የምናረጋግጥበት እንዲሆን ምኞታቸውን በመግለጽ መልዕክታቸውን ቋጭተዋል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ !!
መልካም አዲስ ዓመት!!
በጋራ እንችላለን!