Yonas tesfaye

Yonas tesfaye Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Yonas tesfaye, College & University, Dire Dawa.

04/06/2026

አንድ ጥቁር አሜሪካዊ ሚሊዮን ዶላሮችን በመስረቅ ወንጀል ተከስሶ የአምስት ዓመት እስር ተፈረደበት። ቅጣቱን ከተቀበለ ከአንድ ዓመት በኋላ አባቱ ደብዳቤ ይልክለታል፦«ውድ ልጄ በእርጅናዬና በሕመሜ ጊዜ ለምን ብቻዬን ተዉከኝ፤ ታውቃለህ የእርሻ ወቅት ደርሷል መሬቱን ለመቆፈርና ድንች ለመተከል የሚረዳኝ ሰው ከአጠገቤ የለም። ድንች መትከል ቀላል ነው ነገር ግን በዚህ አቅሜ መቆፈር አልችልም። ዛሬ ላይ አንተ ታስረሃል እና እንደምንም መሞከሬ የማይቀር ነው። በፈጣሪ ፈቃድ እንደገና እንገናኛለን ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።»

ልጅም ከእስር ቤት እንዳለ ለአባቱ መልሶ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጻፈለት፦«የእኔ ውድ አባት እባክህን አሁን ላይ መሬቱን መቆፈር የለብህም። የሰረቅኩትን ገንዘብ በጠቅላላ የእርሻ መሬቱ ላይ ስለቀበርኩት አንተ ላይ አደጋ ያመጣብሃል። ስለዚህ እስከምፈታ ድረስ ጠብቅ።»

በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ውስጥ ሆነ ወደውጭ የሚተላለፍ የእስረኞች ደብዳቤ ስለሚነበብ ምስጥሩ ወዲያው ተደረሰበት። በማግስቱ ጠዋትም ከመቶ በላይ ፖሊሶች ወደ አባቱ ቤት በመሄድ አንድም ሳይቀር የእርሻውን መሬት ቆፋፈሩት። ቢሆንም ግን ለሰዓታት ቢቆፍሩ ምንም አላገኙም ነበር።

ከሦስት ቀን በኋላ ልጁ ለአባቱ ድጋሚ ደብዳቤ ጻፈለት፦«ውድ አባቴ የላኩልህን የሰው ኃይሎች እንደተጠቀምክ ተስፋ አደርጋለሁ። አሁን ድንች መትከል ትችላለህ።» 🤗

28/05/2026

ደብረ ምጥማቅ ምን ማለት ነው?
ግንቦት -21 ለምን ይከበራል)

የግንቦት-21 ደብረ ምጥማቅ ማርያም ታሪክ(ይነበብ)

ግብጽ በምትገኘው በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በተሠራችው ደብረ ምጥማቅ ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ ድንግል ማርያም ከግንቦት ፳፩/21 ጀምሮ እስከ ፳፭/25 ቀናት በተከታታይ በመገለጧ ሕዝበ ክርስቲያኑ በዓሏን ያከብራሉ፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ምድረ ግብጽና ኢትዮጵያ በተሰደደች ጊዜ በአሁኑ ጊዜ ደብረ ምጥማቅ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ዐርፈው ነበር:: ጌታችንም ቦታውን ባርኮ የእርሷ መገለጫ እንዲሆን ቃል ኪዳን ገብቶላት ስለነበር ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት በዓት ሆነ:: በደብረ ምጥማቅም እመቤታችንም ቅድስት ድንግል ማርያም ብርሃን ተጎናጽፋና በሠራዊት መላእክት ታጅባ ተገልጣለች፤ በዚያን ጊዜም ሱራፌል ማዕጠንታቸውን ይዘው ሰገዱላት፤ እንዲህ እያሉም አመሰገኗት፤ ‹‹አብ በሰማይ አይቶ እንዳንቺ ያለ አላገኘም፤ ባንቺም ሰው ሆነ፡፡›› (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ /21ገጽ. ፫፻፲፰/318)

ሰማዕታትም እንደየክብራቸው ማዕረግ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ሊሰግዱ ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው ወደ እርሷ ቀረቡ፤ በመጀመሪያ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሁሉም ቀድሞ ከሰገደላት በኋላ ሌሎቹም በተመሳሳይ መልኩ ሰገዱላት፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዮስ በዱሪ ፈረስ ተቀምጦ ወደ እርሷ በመምጣት ሰገደላት፡፡ ጻድቃን በአንድነት ቀርበው ለክብሯ ሰገዱላት፤ ቀጥሎም በንጉሥ ሄሮድስ በግፍ የተገደሉት ሕፃናት ለእርሷ ሰገዱ፤ በደስታና በፍቅርም ተጫወቱ፡፡ በዚያ የተሰበሰቡትም ክርስቲያኖች፣ እስላሞችና አረማውያን ይህን በአዩ ጊዜ ደስታ ሞልቶባቸው በተለየ ዓለም ያሉ ይመስላቸው ነበር፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ ገጽ. ፫፻፲፰/318)

አባ ጽጌ ድንግልም በደብረ ምጥማቅ በታላቅ ክብር ለምእመናን የታየችው የአምላክ እናት የድንግል ማርያምን መገለጥ በማኅሌተ ጽጌ ድርሰቱ እንዲህ በማለት ገልጾታል፤ ‹‹አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ፣ ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ፣ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ፣ ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሁ መዓልተ፣ ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ፤ የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለአምስት ቀናት ያህል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያህል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው፡፡›› (ማኅሌተ ጽጌ)

በደብረ ምጥማቅ ከተሰበሰቡት ሕዝብ መካከል እናትና አባታቸው፣ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ባልንጀሮቻቸው የሞቱባቸው ሰዎች ቅድስት ድንግል ማርያም እንድታሳያቸው በለመኗት ጊዜ እንደ ቀደመ መልካቸው አድርጋ ታሳያቸው ነበር፡፡ አንዳንዶች ደግሞ መሀረባቸውን ወደ ላይ በሚወረውሩት ጊዜ እርሷ የወደደቻቸው እንደሆነ በእጅዋ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች፤ ሁሉም ለበረከት ይካፈሉታል፡፡ እነርሱም ወደ ቤታቸውም ለመሄድ በሚፈልጉ ሰዓት ተሰናብተውና በተባርከውም ይሄዳሉ፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩/21 ገጽ. ፫፻፲፱/319)

የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች እመቤታችን ድንግል ማርያምን ያዩባቸው ቀናት አረማውያኑ ያመኑበት፣ የበደሉት በምልጃዋ ቸርነትን ምሕረትን ያገኙበት፣ ያመኑት ደግሞ የተባረኩበት ዕለታት ነበሩ፡፡ ሕዝቡ እርሷን ተመኝተው ያጡት ወይንም ጠይቀው ያልተፈጸመላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ጻድቃን፣ ሰማዕታት፣ ደናግል፣ መነኮሳት መላእክትና ሊቃነ መላእክትም ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበር::

ከዚህ በኋላ በዘመናት ይኖሩ የነበሩ ቅዱሳን የአምላክን እናት ለማየት ብዙዎች ተመኝተዋል፤ የመልክአ ማርያም ደራሲ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ የአምላኩን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን ፊቷን ለማየት ሽቶ ‹‹ሰላም ለመልክእኪ ዘተሠርገወ አሜረ ዘያበርህ ወትረ ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ አርእዪኒ ገጸ ዚኣኪ ማርያም ምዕረ ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ፤”
ዘወትር የሚያበራ ፀሐይን ጌጥ ላደረገ መልክሽ ሰላምታ ይገባል፤ ፍቅርን የምትመርጪ (የምታስቀድሚ) አንቺ የምወድሽ ማርያም ሌላ የማይሰማው ነገርን እነግርሽ ዘንድ አንድ ጊዜ ያንቺን ፊት ግለጪልኝ (አሳይኝ)›› በማለት ተማፅኗታል፡፡ (መልክአ ማርያም)

ነቢዩ ዳዊት ‹‹ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኲሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር፤ የምድር ባለጠጎች አሕዛብ ሁሉ በፊትሽ ይማለላሉ›› በማለት ትንቢትን እንደተናገረላት በርካት ቅዱሳን ሰዎች ቅድስት ድንግል ማርያምን ተገልጻላቸው ለማየት ተመኝተዋል፤ ልመናቸው ተሰምቶላቸው የአምላክ እናት ተገልጻላቸው ፊቷን ለማየትን ክብሯን ለመግለጥ ቅዱሳን አባቶች፣ ጻድቃን ሰማዕታት በቅተዋል፡፡ ይህም የሆነው በፍጹም ልቡናቸው በመማፀናቸውና በፍጹም ትጋት የጌታቸውን እናት ሲያገለግሉ በመኖራቸው እንደሆነ የጻድቃኑ ገድል ምስክር ነው፡፡ እነርሱም ሌት ከቀን ምኞታቸው ይሳካላቸው ዘንድ በጸሎት ይማፀኑ ነበር፡፡ (መዝ. ፵፬/40፥፲፪/12)

እመቤታችን ድንግል ማርያምም ጸሎታቸውን ሰምታ ያሰቡትን ትፈጽምላቸው ነበር፤ ምኞታቸው ከተሳካላቸው ቅዱሳን አባቶች መካከል አባ ይስሐቅ አንዱ ነው፤ ይህ ቅዱስ አባትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በፍጹም ልቡናው ይወዳት ስለነበር ለሰባት ዓመታት አምላኩን ክብርት እናቱን ያሳየው ዘንድ በጸሎቱ ተማጸነ፡፡ ዘወትር ከሠርክ ጸሎት በኋላ ሌሎች መነኮሳት ለመኝታ ወደ የበዓታቸው ሲሄዱ አባ ይስሐቅ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕሏ ፊት ቆሞ ሦስት መቶ ስግደትን እየሰገደ ይማፀን ነበር፡፡ ከስግደቱም ጋር ‹‹ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ አርእየኒ እመከ አሐተ ሰዓተ፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአንዲት ሰዓት እናትህን አሳየኝ›› እያለ ይጸልይ ነበር፡፡ በእንደዚህም ሁኔታ ለሰባት ዓመት ከቈየ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በታላቅ ግርማ ተገለጸችለት፤ የልቡም መሻት ምን እንደሆነ ጠየቀችው፤ አባ ይስሐቅም የርሷን ገጽ ያዩ ዐይኖቹ ሌላ ነገርን ማየት እንደማይሹ ነገራት፤ ከተወደደ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ እንድታማልደውም ተማጸናት፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምም ልመናውን ተቀበለች፤ ከዚያም በኋላ የዕረፍቱ ቀን ከሦስት ቀን በኋላ መሆኑን አሳወቀችው፤ ባርካውም ወደ ሰማይም በክብር ዐረገች፤ ይህ ቅዱስ አባት ይስሐቅም እርሷን ካየ በሦስተኛው ቀን ዐረፈ፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ታኀሣሥ ፳፩/21 ገጽ.፬፻፺፪/492)

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ ተገልጣ የሕዝቡን ምኞት እንደፈጸመችላቸው የእኛንም በጎ መሻት ትፈጽምልን፤ አሜን፡፡
ጉባኤ ቤት-Gubae bet
Zekarias Deribe Alemu
fans
#ኦርቶዶክስለዘለዓለምትኑር
#ጉባኤቤት
#ኦርቶዶክሳዊ


ዛሬ 2 ኛ ዙር ጉቢያችን በሰላም ተጠናቀቀ
24/05/2026

ዛሬ 2 ኛ ዙር ጉቢያችን በሰላም ተጠናቀቀ

124 likes, 4 comments. “ #ሄኖክሶልያና፳፩አቡቀለምሲስ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 @መሠረተ ሕይወት .....

15/05/2026

በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የመሶብ (MESOB) የአገልግሎት ማዕከል ስለሚሰጡ አገልግሎቶች

የመሶብ (MESOB) የአንድ ማዕከል የአገልግሎት ስርዓት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የሚሰጡ የትራንስፖርት አገልግሎቶችን ቀልጣፋ፣ ግልጽ፣ ዘመናዊ እና ከብልሹ አሰራር የጸዳ ለማድረግ የተዘረጋ የአገልግሎት ማዕከል ነው።

ማዕከሉ ተገልጋዮች በተለያዩ ቢሮዎች መዘዋወር ሳያስፈልጋቸው በአንድ ቦታ ፈጣንና የተቀናጀ አገልግሎት እንዲያገኙ በማስቻል የጊዜና የወጪ ቁጠባ እንዲኖር አድርጓል።

የመሶብ (MESOB) የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶች

1. የንግድ የመንገድ የህዝብ ትራንስፖርት ኦፕሬተርነት የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ መስጠት

ይህ አገልግሎት በህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ ለመስራት ለሚፈልጉ ኦፕሬተሮች የሚሰጥ ሲሆን፣ ድርጅቱ ወይም ግለሰቡ በህግ የተቀመጡ መስፈርቶችን አሟልቶ መገኘቱን ያረጋግጣል።

2. የንግድ የመንገድ የህዝብ ትራንስፖርት ኦፕሬተርነት ፈቃድ እድሳት

የተሰጠ ፈቃድ የጊዜ ገደቡ ሲያበቃ ተገልጋዮች ፈቃዳቸውን በወቅቱ እንዲያድሱ የሚያስችል አገልግሎት ነው።

3. የንግድ የመንገድ ጭነት ትራንስፖርት ኦፕሬተር የአደረጃጀትና ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ መስጠት

በጭነት ትራንስፖርት ዘርፍ የሚሰሩ ኦፕሬተሮች በህጋዊ እና በቴክኒክ መስፈርቶች መሰረት ብቁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ፈቃድ ነው።

4. የንግድ የመንገድ ጭነት ትራንስፖርት ኦፕሬተር ፈቃድ እድሳት

ነባር የጭነት ትራንስፖርት ኦፕሬተሮች የፈቃዳቸውን ትክክለኛነት በመጠበቅ በህጋዊ ሁኔታ ስራቸውን እንዲቀጥሉ የሚሰጥ አገልግሎት ነው።


5. የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ትራንስፖርት መግቢያ ፈቃድ መስጠት

በዓለም አቀፍ ወይም ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ትራንስፖርት ስራ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎችና ኦፕሬተሮች የሚሰጥ ፈቃድ ነው።

6. የድንበር ተሻጋሪ መግቢያ ፈቃድ እድሳት

የተሰጠው የድንበር ተሻጋሪ ፈቃድ በጊዜው እንዲታደስ የሚያስችል አገልግሎት ነው።

የመሶብ (MESOB) አገልግሎት ጠቀሜታዎች

1. ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት
ቀደም ሲል ቀናት ወይም ሳምንታት ይወስዱ የነበሩ አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል በፍጥነት እንዲጠናቀቁ በማድረግ የጊዜ ፣ወጪ እና ጉልበት መቆጠብ አስችሏል፡፡

2. ግልጽነትና ተጠያቂነት
ተገልጋዮች ስለሚፈልጉት አገልግሎት የሚያስፈልጉ ሰነዶች፣ የአገልግሎት ሂደቶች እና ክፍያዎችን አስቀድመው እንዲያውቁ በመደረጉ ግልጽ የአሰራር ስርዓት ተፈጥሯል።

3. የዲጂታል አሰራር መዘርጋት
የወረቀት ስራዎችን በመቀነስ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር በመዘርጋቱ የመረጃ አያያዝ ቀላልና ዘመናዊ ሆኗል።

4. የደንበኞች እርካታ ማሳደግ
የደንበኞች አቀባበል ስርዓት እና የእንግዳ ማረፊያ ቦታዎች እንዲሻሻሉ በመደረጉ ተገልጋዮች የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል።

5. የኦንላይን አገልግሎት ተደራሽነት
በቴክኖሎጂ የታገዘ ስርዓት በመሆኑ ተገልጋዮች በአካል ሳይገኙ መረጃ ማግኘት፣ ቀጠሮ መያዝ እና አንዳንድ አገልግሎቶችን በኦንላይን ማከናወን ይችላሉ።

የመሶብ (MESOB) አላማ
የሞስብ አገልግሎት ዋና አላማ በትራንስፖርት ዘርፍ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ፣ ግልጽ እና ተጠያቂ የአገልግሎት ባህል በመፍጠር ለተገልጋዮች ቀላልና ፈጣን አገልግሎት ማቅረብ ነው።

30/04/2026
07/04/2026

8611 likes, 41 comments. “ሶስተኛው ቀን ዕረቡ ምክረ አይሁድ ይባላል ተራኪ ዘላለም ሀይሉ”

07/04/2026

9154 likes, 62 comments. “በህማማት ማማተብ ይቻላል #ኦርቶዶክስ #ሰሞነሕማማት #ኦርቶዶክስ⛪ተዋህዶ⛪ለዘለዓለም🙏ትኑር🙏 🇪🇹🇪🇹🇪🇹....

27/02/2026

ሦስተኛው ሳምንት " #ምኲራብ" ይባላል። በዚህ ሳምንት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኲራብ ያስተማራቸውን ትምህርቶችና የገለጻቸውን ተአምራት በስፋት ታስባለች።

ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፦ ጌታችን ወደ ምኲራብ ገብቶ የሚሸጡትንና የሚገዙትን "ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፤ እናንተ ግን የሌቦች ዋሻ አደረጋችኋት" (ማቴ. 21:13) በማለት አስወጥቷቸዋል።

ይህም ሰውነታችንና ቤተ መቅደሱ ለጸሎትና ለቅድስና ብቻ የተለዩ መሆን እንዳለባቸው ያስተምረናል።

የምኲራብ ትምህርት፦ ጌታችን በምኲራብ ሲያስተምር ሕዝቡ በትምህርቱ ይደነቁ ነበር፤ እንደ ጻፎቻቸው ሳይሆን እንደ ባለሥልጣን ያስተምራቸው ነበርና።

ሰውነታችን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነው፦ ቅዱስ ጳውሎስ "የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ በእናንተ እንዲኖር አታውቁምን?" (1ቆሮ. 3:16) እንዳለ፣
ሕይወታችን ከኃጢአት እርኩሰት ልንጠብቀው ይገባል። ኃጢአት ልክ እንደ ነጋዴ በልባችን ገብቶ መንፈሳዊነታችንን እንዳያረክሰው ሁልጊዜ ንቁ መሆን አለብን።

የዕለቱ መዝሙር (የቅዱስ ያሬድ)፦ "ቦአ ኢየሱስ ምኲራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት..."
(ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኲራብ ገባ፤ የሃይማኖትንም ቃል አስተማረ።) የሚል ነው።

የምኲራብ ጌታ እግዚአብሔር ሰውነታችንን ለቅድስናው ማደሪያ ያድርግልን። በዚህ የተቀደሰ የጾም ወቅት ከክፋትና ከርኩሰት ነጽተን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ያድርሰን። አሜን።

በዲ/ን አየለ

#ምኲራብ #ዐቢይ #ጾም

26/02/2026

25.6K likes, 1119 comments. “ሹፌሮች እየሞከሩ ነው”

24/08/2023

Address

Dire Dawa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yonas tesfaye posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share