22/06/2025
#በመጽሓፍ ቅዱስ ውሰጥ አሰደንጋጭ ባለ ታሪኮችና ድርጊቶቻቸው❗🙆
1. አዳምና_ሔዋን፦ የመጀመሪያዎቹ ሰዎችና በእነርሱ አለመታዘዝ የሰው ዘር ሁሉ በስቃይ መኖሩ።🙆
2. አቤልና_ቃኤል፦ ወንድማማቾች፣ በመሥዋዕታቸውና ቃኤል አቤልን በመግደሉ ይታወቃሉ።❗😭
3. ማቱሳላ፦ በጣም ትልቁን የእድሜ ቁጥር የያዘው ሰው (969)።🙆
4. ሄኖክ፦ በ365 ዓመቱ መነጠቁና እስካሁን በሕይወት መኖሩ።❗
5. ኖኅ፦ ከጥፋት ውኃ የሚተርፍበትን መርከብ በመሥራቱ፣ እና የሰው ዘር የቀጠለበት ሰው መሆኑ።❗🙆
6. አብርሃም፦ በእምነቱና በመታዘዙ፤ የግርዛት ሕግን በመቀበሉ።❗🙆
7. ይስሐቅ፦ መሥዋዕት ለመሆንና ለመታረድ ፈቃደኛ የሆነ ታዛዥ ልጅ በመሆኑ።❗
8. ያዕቆብ፦ ለበረከትና ለብኩርና በመታገሉ፣ በአፍቃሪነቱና የ12 ነገደ እስራኤል አባት መሆኑ።❗
9. ዮሴፍ፦ ሕልመኛነቱ፣ ሕልም ፈቺነቱ፣ ታማኝነቱና ያገኘው ሥልጣን።❗
10. ሙሴ፦ የመጀመሪያው የእስራኤል መሪና ሕግ ተቀባይ፣ ሥርዐት ሠሪ።🙆
11. አሮን፦ የሙሴ ወንድምና የመጀመሪያው ሊቀካህን።❗🙆
12. ማርያም፦ የሙሴ ታላቅ እህት፣ ነቢይትና ዘማሪ።❗
13. ኢያሱ፦ ወደ ተስፋይቱ ምድር እስራኤልን ያስገባና ርስት ያከፋፈለ።❗
14. ጌዲዮን፦ በሦስት መቶ ወታደር የምድያማውያንን ሠራዊት ድል በማድረጉ።❗
15. ሳምሶን፦ ፀጉሩ ላይ ባለው ኃይልና በደሊላ መታለሉ።❗
16. ዲቦራ፦ ነቢይትና ፈራጅ።❗
17. ሩት ፦ ሞዐባዊትና የታመነች ሴት❗🙆
18. ሳሙኤል፦ በስእለት የተወለደ የሀና ልጅ፣ የታመነ ነቢይና መስፍን።🙆❗
19. ሳዖል፦ ከብት ፍለጋ በሄደበት ድንገት የተቀባና የእግዚአብሔርን ቃል ባለመስማቱ ንግስና የተወሰደበት የመጀመሪያው የአይሁድ ንጉሥ።❗
20. ዳዊት፦ በዘማሪነቱ፣ በንግስናው፣ በንስሐ ሕይወቱና ጎልያድን በመጣሉ።❗
21. ሰሎሞን፦ በጥበበኛነቱና የመጀመሪያውን የእግዚአብሔር መቅደስ የሠራ በመሆኑ።❗🙆
22. ኤልያስ፦ እስካሁን ያልሞተና የተነጠቀ፣ ሰማይን የዘጋ፣ እሳት ያወረደ ታላቅ ነቢይ በመሆኑ።❗🙆
23. ኤልሳዕ፦ የኤልያስ ደቀመዝሙር፣ ብዙ ተአምራትን ያደረገ።❗🙆
24. ኢዮብ፦ ጻድቅና የመከራ ሰው፤ በትእግስቱ የሚደነቅ ሰው።😭❗
25. መልከ_ጼዴቅ፦ ንጉሥም ካህንም የሆነ፣ ከአብርሃም አስራትን የተቀበለ፣ የኢየሱስ ምሳሌ የሆነ ሰው።😭
26. ኢሳይያስ፣ ኤርምያስ፣ ሕዝቅኤልና ዳንኤል፦ ታላላቅ ነቢያት ።❗
27. ሆሴዕ፦ የእስራኤል ነቢይና አመንዝራዋን ሴት እንዲያገባ በጌታ የታዘዘ ሰው።❗
28. ዮናስ፦ የዋሁ ነቢይና ከእግዚአብሔር የኮበለለው፣ በዓሣ አንበሪ ሆድ ውስጥ ሦስት ቀን ያደረው፣ የጌታ ኢየሱስ ምሳሌ የሆነ ሰው።❗
29. መርዶክዮስ፦ የአስቴር አጎትና ታላቅ የእምነት ሰው፣ የመጽሐፈ አስቴር ጸሐፊ።❗🙆
30. ነህምያ፦ የእስራኤልን ቅጥር የሠራ ታላቅ መሪ።❗🙆
31. ዕዝራ፦ አንባቢ፣ የሕጉ ተርጓሚና ፀሐፊ።❗
32. ሎጥ፦ የአብርሃም የወንድም ልጅ፣ ከሰዶምና ከገሞራ ጥፋት ያመለጠ፣ ከልጆቹ አሞንና ሞዐብን የወለደ።🙆❗
page follow,like,share በማድረግ ይተባበሩ።❗