Ermias legesse

Ermias legesse Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ermias legesse, College & University, Abosto, Nazareth.

27/12/2022

አትምሰሉአቸው
ዋጋ ቢስ

ማቴዎስ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ለሰዎች ትታዩ ዘንድ ምጽዋታችሁን በፊታቸው እንዳታደርጉ ተጠንቀቁ፤ ያለዚያ በሰማያት ባለው አባታችሁ ዘንድ ዋጋ የላችሁም።
² እንግዲህ ምጽዋት ስታደርግ፥ ግብዞች በሰው ዘንድ ሊከበሩ በምኩራብ በመንገድም እንደሚያደርጉ በፊትህ መለከት አታስነፋ፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።
³-⁴ አንተ ግን ምጽዋት ስታደርግ ምጽዋትህ በስውር እንዲሆን ቀኝህ የምትሠራውን ግራህ አትወቅ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።
⁵ ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይን ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።
⁶ አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።
⁷ አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ በከንቱ አትድገሙ።
⁸ ስለዚህ አትምሰሉአቸው፤ ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና።

As long as Europe 🇪🇺 and America 🇺🇸 Control our Money, they will Control our Economy: We need African Common Currency ba...
05/10/2021

As long as Europe 🇪🇺 and America 🇺🇸 Control our Money, they will Control our Economy: We need African Common Currency backed by our Resources not by Dollar or by Euro

Africa may never be able to build any of the prosperous economies we built in the past because we are nearly working entirely to support the economies of others while every value we have on our land is made to be taken away for free.

You may like to ask the next person to you this question: "why do African countries sell their product to America in Dollars, to EU countries in Euros, and to China in Yuan?"

The obvious answer you are likely to receive is: Because we need foreign exchange!

But, if we need foreign exchange (their currency) to demand for what they have of which we are in need, why don't they also need foreign exchange (our currency) to demand for what we have of which they are in need?

We want foreign currency, they want our value.

We have been Programmed into thinking that their paper is either more valuable or equally in value to our valuable resources and goods. But our paper worth nothing to their resources and goods.

But, the truth of the concept of paper money is that it only worth the value of goods or resources you own not that of others. This is the reason why Britain sells her products to US, EU, Africa or any other country in the British Pounds Sterling, Germany sells her products in Euros to Everyone including the US and China. When China want to own a share of the US Economy, it had to produce goods and values and sell them on the US market to obtain US dollars in order to use that dollar to obtain a share of the US economy through bonds and bills. China doesn't sell her product to America and pack US dollars to Chinese.

Our economic management teams must begin to understand that, no matter how little our resources may look in their eyes in their understanding, they are not valuess so they must be sold in our currencies. To allow them to be sold in the currencies of others means that we simply do not know that they even have any value at all.

The government of the African Continental Unity Party will Create an African Continental Currency which will be backed by the huge natural, material, and knowledge resources found in Africa; it is in this currency in which all African capital shall be traded in.

Join the African Continental Unity Party, Register your membership at www.africanacup.org

25/09/2021

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!

ስለ መስቀል በዓል ስናነሣ አንድ መታሰብ ያለበት ጉዳይ አለ። ከፈተና በኋላ ድል፣ ከጨለማ በኋላ ብርሃን፣ ከመውደቅ በኋላ መነሣት እንደሚኖር። የጠፋ ሁሉ ጠፍቶ እንደማይቀ፤ የመስቀሉ ታሪክ ያስተምረናል።

ባለፉት ሦስት ዐሠርት ዓመታት የኢትዮጵያዊነት ስሜት ከልባችን ላይ እንዲፋቅና ስለ ሀገር ያለን ፍቅር ከውስጣችን እንዲጠፋ በብዙ መልኩ ሤራ ተሠርቷል። እርስ በእርስ በጥርጣሬ እንድንተያይ ብዙ ተንኮል ተጎንጉኗል። በደስታም ሆነ በኀዘናችን፣ በድልም ሆነ በችግራችን አንድነትና ኅብረታችንን እንዳናስቀድም ተደርገናል። ምኞትና ፍላጎታችን በክልልና በብሔር ዙሪያ ብቻ ታጥሮ ትልቁን ሀገራዊ ምስል እንዳናስተውል ተሞክሯል። ሳይወዷት የመሯት ጠላቶቿ፣ ኢትዮጵያ በትንሽ በትንሹ እየፈረሰች እንደሆነ እያሰቡ ይደሰቱ ነበር። "አሁን ያለችው ኢትዮጵያ እኛ ብቻ እንድናስተዳደራት የተሠራች ናት፤ እኛ እስከፈቀድን ድረስ የምትኖር፣ በሌላ እጅ ከገባች በቀላሉ የምትፈርስ ናት" እያሉ በዕብሪት አፋቸውን ሞልተው ይናገሩ ነበር። ሕዝባዊ አንድነታችን ላልቶ እንደተበጠሰና እነርሱ በፈለጉ ጊዜ ሀገራችንን በቀላሉ ሊያፈርሷት እንደሚችሉ ደጋግመው ዝተዋል። ዳሩ ግን ሁሉም ነገር እንደተናገሩት አልሆነም። ኢትዮጵያዊነት እንደ ክርስቲያኖች መስቀል የመለያየት አፈር የተጫነው ቢመስልም አልጠፋም። አንድነታችን የሰለለ ቢመስልም አልተበጠሰም። ለሀገር ያለን ቀናዒነት የተዳፈነ ቢመስልም አልቀዘቀዘም ነበር።

ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል በክርስቲያኖች ዘንድ የፈውስና የኃይል ምንጭ ተደርጎ ይታመናል። ለሕመማቸው ፈውስን፣ ለመከራቸው ጊዜ ጽናትን፣ በተሰበሩ ጊዜ ብርታትን፣ በተበታተኑ ጊዜ ኅብረትን አምጥቶላቸዋል። ይኽ ሁኔታ ያላስደሰታቸው የዚያን ዘመን ጨቋኞች ሤራ ሲያስቡ ዋና ትኩረታቸውን ያደረጉት የመስቀሉን ደብዛ ለማጥፋት ነበር። ከሰው ደብቀው ቀበሩት። ቦታውንም የቆሻሻ መጣያ እንዲሆን አዘዙ። ለ300 ዓመታት ከየነዋሪው ቤትና ከየሰው ግቢ ተጠርጎ የሚወጣ ቆሻሻ እየተጣለበት ቆይቶ ግዙፍ ተራሮችን መሰለ። ነገር ግን ክፉዎች እንዲህ ለክፋት መትጋታቸው በመስቀሉ ቤዛነት የሚያምኑትን አላሸነፈም። ተራራ ንደው፣ ቁልሉን ደርምሰው፣ አቧራውን ጠርገው፣ መስቀሉን ከማግኘት አላገዳቸውም።
ባሳለፍነው ዓመት አሸባሪው ጁንታና የኢትዮጵያ ጠላቶች በሐሰት ፕሮፓጋንዳቸው የሀገራችንን ስም ሊቀብሩ ተባብረው ሲሠሩ ነበር። በውሸት የተቀመሙ ዜናዎቻቸውን በሚያሠራጩባቸው ሚዲያዎች አማካኝነት ያልተፈጠረውን ተፈጠረ፣ ያልሆነውን ሆነ እያሉ፣ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ኢትዮጵያ ቀና ብላ እንዳትታይ ዐቅማቸው የፈቀደውን ሁሉ አድርገዋል። ዓላማቸው ግልጽ ነው። የእነርሱ ጥቅም የሚከበረው በእኛ መሸነፍ ውስጥ እንደሆነ ያውቃሉ። በውንጀላዎቻቸው ተሸንፈን ጉልበታችን ሲብረከረክ በቀላሉ እጅ እንሰጣለን፤ ለእኩይ ፍላጎታቸው ተገዥ እንሆናለን ብለው አስበዋል። በተሸናፊነት ሥነ ልቡና ውስጥ ገብተን ዳግም በእግራችን መቆም ካልቻልን፣ ያኔ እስከመጨረሻው የእነርሱ ጥቅም ባሪያዎች ሆነን እንደምንቀር ጠንቅቀው ያውቃሉ። ስለዚህም የቻሉትን ያህል የውሸት ቆሻሻ ሰብስበው፣ የእኛን እውነት የሚጋርድ ግዙፍ ተራራ መፍጠር ችለዋል።

መስቀሉን አርቀው የቀበሩ ሰዎች መስቀሉ ለዘላለም እንደተቀበረ የሚቀር መስሏቸው ነበር። መስቀሉ አፈር ተጭኖት ስለተከለለ ትውስታው ከምድረ ገጽ እንደሚሰረዝ፣ እምነቱ ከክርስቲያኖች ልብ ተፍቆ እንደሚጠፋ አስበዋል። ነገር ግን ሐሳባቸው እውነት የመሰለው እንደ ንግሥት እሌኒ ያሉ ብርቱዎች መስቀሉን ፍለጋ እስኪነሡ ድረስ ብቻ ነው። የእነርሱ ዓላማ ስኬት የተመሠረተው በሌሎች ስንፍና ላይ በመሆኑ፣ ብርቱ ፈላጊዎች ቆርጠው በተነሡ ጊዜ፣ የመስቀሉ መጥፋት ጉዳይ ያከትምለት ጀመር። “ጠፋ”ጠፋ የሚለው ዜና “ተገኘ” በሚለው ዜና ተተካ። እንደተተካም ቀረ።

ንግሥት እሌኒ መስቀሉን ለመፈለግ በተነሣች ጊዜ፣ ነገር ሁሉ አልጋ በአልጋ ሆኖ አልጠበቃትም። መስቀሉ ስለመቀበሩ እንጂ የት እንደተቀበረ እንኳን አታውቅም ነበር። በዙሪያዋ የነበሩ ሰዎችም መንገድ ከመጠቆም ይልቅ ተስፋ በማስቆረጥ የተጠመዱ ነበሩ። የመስቀሉ ጉዳይ ያበቃ ያከተመለት ጉዳይ እንደሆነ ነበር የሚነግሯት። እሷ ግን እጇን አጣጥፋ ከመቀመጥ ይልቅ እምነትና ተስፋዋን ይዛ በመፈለጉ ጸናች። ተስፋ አስቆራጮች የሚናገሩትን ትታ እምነት የጣለችበትን የዕጣን ጢስ ተከተለች። ተከትላም አልቀረች። ጢሱም መስቀሉ የተቀበረበትን ትክክለኛ ቦታ መጠቆም ብቻ ሳይሆን፣ ከብዙ ድካምና ልፋት ታደጋት። የዕጣኑ ጢስ ወደ እውነተኛው ቦታ የሚያደርስ ምልክት ሆናት።
ለዘመናት በሤረኞች ተንኮል ደብዝዞ የጠፋ የመሰለው አንድነትና ኢትዮጵያዊነታችን ወደ ቦታው እየተመለሰ ነው። ይሄንን የሚያሳዩ ምልክቶች ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ መታየት ጀምረዋል። እንደ እሌኒ ያሉ ጀግኖች፣ ሤረኞች የቀበሩት የመሰላቸውን ኢትዮጵያዊነት እያወጡት ነው። ከመላ ኢትዮጵያ፣ አያሌ እሌኒዎች መጥተው ታሪክ እየሠሩ ነው። ድሮ በክልሎች መካከል የነበሩ መሥመር የሳቱ ፉክክሮች አሁን በትብብር ተለውጠዋል። “አትምጣብኝ አልምጣብህ” የሚሉ ክፉ ንግግሮች “ለችግርህ ደራሽ እኔ ነኝ” በሚል ተተክተዋል። በየጓዳችን ተወሽቀን ስለ ጓዳችን ብቻ አብዝተን መጨነቃችን ቀርቶ ዛሬ ሀገራዊ ጥቅማችንን ላለማስነካት በዓለም ፊት በአንድ ድምፅ መናገር ጀምረናል። ኢትዮጵያዊ ማንነታችን በእርግጥም በደማችን ውስጥ ስለመኖሩ አሁን በግልጽ ይታያል። ኅብርነታችን መለያያችን ሳይሆን የአንድነት ጌጣችን መሆኑን እንደ መስቀሉ ከፍ አድርገን አሳይተናል።

አሁን ኢትዮጵያ በየተሠማሩበት መስክ ሉዓላዊነቷን ላለማስደፈር የሚባትሉ ልጆቿ ጥቂቶች አለመሆናቸውን እያየች ነው። ከጠላት ጋር አብረው ከጀርባ የሚወጓት ክፉ ልጆችዋ ዕለት በዕለት ቀን ሲጨልምባቸው፣ ወደ አመድነት ሲለወጡ፤ በተቃራኒው ለክብሯ ለሚጨነቁ ደጋግ ልጆችዋ ፈተናው እየቀለለ፣ የድል ውጋጋን በመታየት ላይ ነው። የጨለማው ጊዜ ተወግዶ ብርሃኑን፣ የፈተና ጊዜ አልፎ ድሉን የምናይበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን አልጠራጠርም። የሤረኞች ምንቸት ወጥቶ፣ የኢትዮጵያዊነት ምንቸት እየገባ ነው።

የመስቀልን በዓል ስናከብር ግዛታዊ አንድነታችንን ለማስጠበቅ በዱር በገደሉ የሚወድቁ እኅቶቻችንንና ወንድሞቻችንን እያሰብን መሆን አለበት። እነርሱ እንደ ደመራው አንድ ሆነው ለኢትዮጵያ የሚሠው ህያዋን ችቦዎች ናቸው። ዛሬ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ተጠብቆ ያለው እነርሱ በሚከሰክሱት አጥንትና በሚያፈሱት ደም ነው። በተመሳሳይ በጁንታው ጥቃት የተጎዱ ዜጎቻችንን አለሁ ልንላቸው፣ ከጎናቸው ልንቆም ይገባል። የከፈሉት ዋጋ ለኢትዮጵያ የተከፈለ ዋጋ ነው። የታመሙት የሁላችንን ሕመም ነው። ከቤት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን መልሶ የማቋቋም፣ የፈረሱ ትምህርት ቤቶችን የመገንባትና የወደሙ ጤና ተቋማትን በምትካቸው የመሥራት ኃላፊነት በእያንዳንዳችን ትከሻ ላይ የወደቀ ነው። ይሄንን ዐውቀን ከአሁኑ ወገባችን አሥረን መነሣት አለብን። ካላጎነበሳችሁ አንረዳችሁም የሚሉ ወገኞች ይኖሩ ይሆናል። ለኢትዮጵያ ሲባል ሐሞትና ከርቤ ለመጠጣት እንገደድ ይሆናል። ጥርሳችን ነክሰንና አንጀታችን አሥረን እንጋፈጠዋለን። ተጋፍጠንም እናሸንፈዋለን።

በዓሉ የሰላም፣ የመረዳዳትና የመተጋገዝ እንዲሆን እመኛለሁ።

በድጋሚ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
መስከረም 15፣ 2014 ዓ.ም

25/10/2020
07/09/2020

Happy New year to Ethiopia Abiy ahmed

Address

Abosto
Nazareth

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ermias legesse posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share