የቡድኸ

የቡድኸ Theological philosophy

11/08/2024

የአቡዬ ልጅ ታምራት ቶላ

ሰሜን ሸዋ ውስጥ የሚገኘው ጥንታዊው የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ከ110 አመት በላይ እድሜ አለው። በአሁኑ ወቅት ምዕመናኑ በአፈር የተሰራውን ቤተክርስቲያን በአዲስ መልክ እያስገነቡት ይገኛሉ። አንዱ አስተባባሪና አጋዥ ደግሞ ታምራት ነው።

ታምራት ቶላ ትውልድና እድገቱ ሰሜን ሸዋ ፥ አለልቱ ወረዳ ሉባዬ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነው። አትሌቱ በማራቶን ሀገራችንን በተደጋጋሚ ወክሎ ውጤታማ ሆኗል። በኦሪገን ወርቅ ፣ በለንደን አለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ በሪዮ ኦሊምፒክ ደግሞ የነሀስ ሜዳሊያን አጥልቋል፤ በግማሽ ማራቶንና በሀገር አቋራጭም ስኬታማ ነበር።

ታምራት የተወለደበትን ቀዬ የማይረሳ በመንፈሳዊ ህይወቱም ጠንካራ መሆኑ ይነገርለታል። እንደ አዲስ ለሚገነባው የአቡዬ ቤተክርስቲያንም ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ተብሏል።

በዚሁ አካባቢ ልምምድ ሲሰራና፣ ሲፀልይ፣ የቤተክርስቲያኒቱን ግንባታ በቅርበት እንደ ባለቤት ሲከታተል እንደነበር ሰምተናል፤ የአካባቢው ማህበረሰብም ታምራትን "የአቡዬ ልጅ" ብለው ይጠሩታል።

11/08/2024


=================
ማንም አያስቆመውም! ነገር ግን የመግቢያ ክፍያ 200 ብር ብቻ እና #ካሜራ ገብተው ፎቶግራፍ በማንሳት እየተዝናኑ ፣የብልፅግናን ስኬት ማድነቅ ይቻላል።! ያለበለዚያ ዙፋኑን በቢላና በሰይፍ መውጣትና ሥልጣን መያዝ አይቻልም። #ስልጣን በምርጫ እና በምርጫ ብቻ ነዉ።


13/07/2024
15/06/2024

እንኳን ለዒድ አል አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!

ኢድ አል አድሃ/አረፋ/ በሙስሊም ማኅበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ክብር ያለው በዓል ነው። ዐቅሙ እና ሁኔታው የፈቀደላቸው ምዕመናን የሐጅ ሥነ ሥርዓትን በመፈጸም ያከብሩታል። ሌሎች ደግሞ በየሀገራቸው በጋራ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ በጸሎት፣ በመደጋገፍና በአብሮነት ያከብሩታል። በሀገራችንም ሙስሊሞች በዓሉን በጸሎት፣ ማዕድን በማጋራት እንዲሁም በደስታ በፍቅር ተጋግዘው ሲያሳልፉ እየያን አድገናል። አብረንም አክብረናል።

የዘንድሮ በዓል ሲከበር ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በመጠየቅ እና በመደገፍ እንዲሁም ዐቅመ ደካሞችን በመንከባከብ እንደሚሆን አምናለሁ።

በዚሁ አጋጣሚ የሀገራችን ሙስሊም ማኅበረሰብ የመደጋገፍ ባህል ከተረጂነት ለመላቀቅ ለምናደርገው ትግል ወሳኝ ዕሴት ነው። እርስ በእርሳችን በመደጋገፍ በተረጂነት ከመታወቅ መውጣት አለብን። ለዚህ ደግሞ በበዓል ጊዜ የምናደርገውን መደጋገፍ የዘወትር ተግባር ማድረግ ነው።

እንደ ሀገር ላለፍንባቸው ችግሮቻችን መፍትሔ የሆነው የሽግግር ፍትሕ እና መፃዒ አብሮነታችንን ለማጎልበት ወሳኝ ለሆነው የሀገራዊ የምክክር ውጤታማነት ሙስሊሙ ማኅበረሰብ የበኩሉን ሀገራዊ ኃላፊነት እንዲወጣ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ።

በድጋሚ እንኳን ለኢድ አል አድሃ/አረፋ/ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ፣ በዓሉ የሰላም የፍቅር የደስታ የአንድነት በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ኢድ ሙባረክ

15/06/2024

በህጋዊ ህገወጥ ና
በህገወጥ ህጋዊ መካከል ያለውን ልይነት ንገሩኝ ወይም አስረዱኝ 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

Happy Easter for ethiopian
04/05/2024

Happy Easter for ethiopian

09/04/2024
22/03/2024

Address

Nefas Silk

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቡድኸ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The University

Send a message to የቡድኸ:

Share