31/03/2026
የሚቶ ወረዳ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ለሚቶ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን በኢትዮኮደርስ አተገባበር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ
የሚቶ ወረዳ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ለሚቶ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን በኢትዮኮደርስ አተገባበር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጪያ ስልጠና ተሰጥቷል
በስልጠናው የሚቶ ወረዳ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ንጉሴ ፍቃዱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን እንደዚህ አይነቱ ስልጠና የክህሎት ችግር ላለባቸው መመህራን ትልቅ መፍትሔ የሚሆን ነዉ የሉ ሲሆን ቀጣይነት በለው ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በተጨማሪም በቀጣይ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተናን በኦንላየን ለመስጠት የሚያስችል የኮምፒውተር ቅድመ ዝግጅት ከዚህ ቀደም የተበላሹትን ኮምፒውተሮችን የሚቶ ወረዳ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ባለሙያዎች በመጠገን ለሚቶ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ም/ል ር/መምህር ለአቶ በድሩ ከማል ርክክብ የተደረገ ሲሆን የቀሩትንም በቅርብ ግዜ ውስጥ ጥገናቸው አልቆ እንደሚያስረክቡ ገልፀዋል